No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Friday 17 August 2012

የአቶ በረከት ስምዖን ሽሙጥ: ከፍቅሬ ዘለቀው፣ ኖርዎይ

በባራክ ኦባማ አስተዳደር ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ በደቪድ ካምፕ ዋሽንግቶን የዓለም ምግብ 
ዋስትናና ፖለቲካ ፈተናዎች በሚል ለተዘጋጀው የግንቦት 18፣ 2012 የቡድን ስምንት 
(G8- summit) የመሪዎች ጉባኤ አምባገነኑ መለስ ዜናዊ በአለቃቸው ተጋብዘው 
ለመሳተፍ ከውጪ ይጠብቋቸው የነበረውን የኢትዮጵያንን ቁጣ በጓሮ በር ሸሽተው 
በመግባት በስብሰባው ላይ ዲስኩር እያሰሙ እያሉ ነበር የመላውን ኢትዮጵያ ህዝብ 
ድምፅ ባነገበ ጀግናና አለኝታችንአበበ ገላው ቁጣ ቀልባቸው ተገፎ ከዕለቱ ጀምሮ 
ምናልባትም ለፍፃሜ ህልፈተ-ህይዎታቸው በሽታ ተዳርገው፣ ከአንድ ወር 
በሗላም በገረጣ ፊትና በከሳ ሰውነት በድጋሜ በሜክሲኮ ዋና ከተማ በኢንዱስትሪ 
በበለፀጉ አገሮች ስብሰባ ላይ ለመጨረሻ ጊዜ የታዩት።

እስካሁንም የእሳቸው ደብዛ መጥፋት በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ደስታና ስጋት የተቀላቀለበት 
ስሜት ፈጥሮ መነጋገሪያ የሆነ ቢሆንም፣ የጠቅላይ ሚኒስቴሩ እንዲህ መሆን ደግሞ 
በአንድ ግለሰብ ለምትመራ አገር ወይም በህገ አራዊት ለምትተዳደር አገር በአፍሪካ ቀንድ 
አለመረጋጋትን ሊፈጥር ይችላል በሚሉና ሐሳባቸውን በጊዜያዊ ጥቅምና መረጋጋት ላይ 
ያተኮሩትን የምዕራባዊያን ወዳጆቻቸውንም ስጋት መፍጠሩ አገር በቀል የዜና አውታሮች 
ብቻ ሳይሆኑ የዓለም አቀፉንም ትኩረት በመሳብ የዕለት ከዕለት መነጋገሪያ ርዕስ በመሆን 
ላይ ይገኛል። 

ESAT Ethiopian News August 17, 2012


ጄነራል ሳሞራ የኑስ በጠና ታመው ትላንት ምሽት ኢትዮጵያን ለቀቁ


የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ አይታወቅም። ጠቅላይ ሚንስትሩ ይዘውት የነበረውን የጠቅላይ ጦር አዝዥነትን ሚና በማን ኃላፊነት ላይ ሊወድቅ እንደሚችል ግልጽ አልነበረም። ይህንን ክፍተት ለመሙላት ከጠቅላይ ሚንስትሩ ቀጥሎ የጦር አዛዥነቱን ሚና ጄነራል ሳሞራ የኑስ ተክቶ ይሰራል፤ ተብሎ ግምት ሲሰጥ ቢቆይም…አሁን ግን ሳሞራ የኑስም በድንገተኛ ህመም ስራቸውን ያቆሙ መሆኑን ለማወቅ ችለናል። ይልቁንም በትላንትናው ምሽት ህመማቸው ስለጠና፤ ለህክምና ወደውጭ አገር ለቀው ወጥተዋል።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ሰራዊት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ ሆኖ፤ አመራሩን ሌ/ጄነራል ሰዓረ መኮንን እና ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ በመስጠት ላይ ናቸው። ከጄነራል ሳሞራ የኑስ ድንገተኛ ህመም በኋላ ሌ/ጄኔራል ፀዓረ በተለይ የትግራው / የህወሃት ጄነራሎች ጋር ስብሰባ ማድረጉንና ሰራዊቱ በተጠንቀቅ ላይ ሆኖ፤ በተለይ በኮሎኔል ደረጃ የሚገኙ የብአዴን ጦር መኮንኖችንን በቅርብ እንዲከታተሉ መመሪያ ተሰጥቷል። በዚህም መሰረት በተለይ የቀድሞ የኢህዴን ታጋይ የነበሩ እና አሁን በብአዴን ውስጥ በጦር

አይታክቴው ታማኝ በሲድኒ


አብይ ዮሃንስ አፈወርቅ 
በአውስትራሊያ የኢሳት ርዳታ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በደማቅ ሁኔታ ተጀመረ
       በዓለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ቀልብ ጠልፎ አማራጭ ሜዲያነቱን ያረጋገጠውን ኢሳትን
ለመርዳት በተለያዩ የአውስትራሊያ ከተሞች የተያዘው የገቢ ማሰባሰብ ፕሮግራም ትላንት እሁድ ኦገስት 12
ቀን 2012 ዓ.ም. እጅግ በደመቀ ሁኔታ በሲድኒ ተጀምሯል።       ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሲድኒ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን
 በጋለ ስሜት ተሞልተው ዝግጅቱን ያደመቁት ሲሆን ተወዳጁ አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነም እንደተለመደው
ሁሉ በተባ አንደበቱ ወሳኝ የሆኑ አገርኛ ጉዳዮችን እያነሳ በመረጃ የተደገፉ ትንታኔዎችን አቅርቧል።
       አክቲቪስት ታማኝ በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመገኘት የበቃው ከአራት ቀናት በላይ የፈጀ መኝታ

የፓትርያርክ ጳውሎስ ገመና ፣ በደሎች ፣ መታሰቢያና ውርሶች


አዲሱ ተስፋዬ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን እስካሁን አምስት ኢትዮጵያውያን ፓትርያርኮች ተሹመው አልፈዋል:: ፓትርያርኮቹ የሚታወሱበት የተለያየ ባህርይና መታወሻan article about Abune paulos EGYPT ETHIOPIA AFRICAN UNION SIDELINES
ነበሯቸው:: ሰኔ 21, 1951 አ.ም የተሾሙት የመጀመርያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ እጅግ ሲበዛ ሊቅ እንደነበሩ ታሪክ ያስታውሰናል [1] :: ቤተ ክርስትያኒቱ የራስዋን ልጆች ፓትርያርክ አድርጋ እንድትሾም ፣ ከፍተኛ ተጋድሎ አካሂደው ቤተክርስትያኗ ነጻነት እንድታገኝ አድርገዋል[2] :: ህዝበ ክርስትያኑም ክርስትናውን እንዲያጸና ብዙ ታግለዋል :: ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅም የሳቸው ውጥን ነው [3] :: እሳቸው ሲያርፉ የተሾሙት ሁለተኛው ፓትርያርክ አቡነ ቴዎፍሎስም የሳቸውን መስመር ተከትለው ለቤተክርስትያኒቱ ከፍተኛ አስተዋጾ አበርክተዋል [4] :: በተለይም ኢኮኖሚም የዳበረ አቅም እንዲኖራት በርካታ መሰረተ ልማቶችን አስገንብተዋል :: “እግዚአብሄር የለም” የሚለውንም የግፈኛው ደርግን አውራዎች በመቃወም ሰማእትነትን ተቀብለዋል [5]:: ሶስተኛው ፓትርያርክ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለእግራቸው እንክዋን ጫማ ለማጥለቅ የሚለመኑ ፣ በጾም ብዛት እንዳይሞቱ የሚሰጋላቸው ፣ አለምን ከነምኞቱ የሰቀሉ እውነተኛ መናኝና የእግዚአብሄር ሰው ነበሩ [6]:: በወቅቱ የነበረው የኢሰፓ መንግስት አዲስ አበባ የሚገኘውን አንድ ቤተ ክርስትያን “ዘግቼ ሙዚየም

Thursday 16 August 2012

ESAT Ethiopian News August 16, 2012


አወዛጋቢው አቶ መለስ ከያራ አግኝተውት የነበረው ሽልማት በሙስና የተገኘ እንደነበር ተጋለጠ



(ፍኖተ ነጻነት ጋዜጣ)
ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በ1997 ዓ.ም በማዳበሪያ አምራችነቱ ከሚታወቀው ያራ ፋውንዴሽን ድርጅት የተቀበሉት የእውቅናና የገንዘብ ሽልማት አሁንም እያወዛገበ ነው፡፡
አቶ መለስ ከድርጅቱ የበላይ አመራር ሚስተር ኢንጌር የተቀበሉት የወቅቱ ሽልማት ድርጅቱ በማዳበሪያ ንግዱ ከኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ያላቸውን የትርፍ ክፍፍል ግንኙነት ለማጠናከር ሆንተብሎ የተሰጠ መሆኑ ተነገረ፡፡
በኖዌይ የሚታተመው አፍተን ፖስት ጋዜጣ ይፋ ባደረገው ስሞነኛ መረጃው ድርጅቱ ከሚያገኘው የተጣራ ትርፍ 30 በመቶ፣ የተፈጥሮ ሀብቱን ለተጠቀመበት (royalty) 4 በመቶ ለባለስልጣናቱ የሚከፍል ሲሆን፣ ካላቸው ድርሻም 5 በመቶ እንደሚያገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እንደ ጋዜጣው ዘገባ አንድ ሦስተኛው የድርጅቱ ትርፍ በአፍሪካ ተወዳዳሪ ወደ ሌለው ጨካኝ ስርዓት ኪስ እንደሚገባ ነው፡፡ የያራ ድርጅት የመረጃ ዳይሬክተር ኤስባን ቱማን ጋዜጣው ስለአዋጭነቱ ለጠየቀው ጥያቄ ሲመልሱ “ይሆናል ብለን እንገምታለን፤ አሁን በጅማሮ ላይ በመሆናችን መገመቱ ግን ያስቸግራል” ብለዋል፡፡

One pope is down and another one is missing in action

Aba Gebremedhin is finally gone. Now he is where he belongs… in hell and burning in the lake of fire.

Let us see what God says about judging false teachers and their collaborators.
“And the devil who had deceived them was thrown into the lake of fire and sulfur where the beast and the false prophet were, and they will be tormented day and night forever and ever.” Revelation 20:10
“Beware of false prophets, who come to you in sheep’s clothing but inwardly are ravenous wolves.” Mathew 7:15
“An instructor of the foolish, a teacher of children, having in the law the embodiment of knowledge and truth— you then who teach others, do you not teach yourself? While you preach against stealing, do you steal? You who say that one must not commit adultery, do you commit adultery? You who abhor idols, do you rob temples? You who boast in the law dishonor God by breaking the law. For, as it is written, “The name of God is blasphemed among the Gentiles because of you.” Romans 2:2-24
“‘I know your works, your toil and your patient endurance, and how you cannot bear with those who are evil, but have tested those who call themselves apostles and are not, and found them to be false.” Revelations:2:2

Ethiopia: Abune Paulos the Fake Patriarch Died

According to Deje Selam blog and many other pro-woyane bloggers the most hated Ethiopian Orthodox Church fake Patriarch (Abune Paulos) is dead.

Ethiopia: Abune Paulos the Fake Patriarch Dies

ESAT Daily Ethiopian News, Washington D.C. August 15, 2012


Wednesday 15 August 2012

Prominent Muslims Detained in Crackdown

Security Forces Arrest Hundreds of Peaceful Protesters; Detainees at Risk

Human Rights Watch
(Nairobi) – The Ethiopian government should immediately release 17 prominent Muslim leaders arrested as part of a brutal crackdown on peaceful Muslim protesters in Addis Ababa, Human Rights Watch said today. A court is expected to rule during the week of August 13, 2012, on whether to bring charges against the detainees who have been held for almost three weeks in a notorious prison without access to lawyers.
Since July 13, Ethiopian police and security services have harassed, assaulted, and arbitrarily arrested hundreds of Muslims at Addis Ababa’s Awalia and Anwar mosques who were protesting government interference in religious affairs, Human Rights Watch said. Many have been released but at least 17 prominent members of the community arrested between July 19 and 21 remain in detention. A number of protesters who have been released told Human Rights Watch that they were mistreated in custody.

መለስ ዜናዊ ከነጥፋት ውሃው ሲታወስ


መለስ ዜናዊ ከነጥፋት ውሃው ሲታወስ
 ከአቢቹ ነጋ
 *1* በተለምዶ ሰው የዘራውን ያጭዳል ይባላል:: ከመልካም ዘር ደግ ነገር ይመረታል እጸበለስን የዘራ መርዝን ያመርታል:: ይህ በሰው ህይወት ዘመን ሁሉ ተፈጻሚ ነው:: ከእባብ ግን የርግብ እንቁላል አይጠበቅም:: መለስ የተባለ ሰው በወጣትነት ዘመኑ ጥሩ የትምህርት ዘር ዘርቶ በታወቀው የጀነራል ዊንጌት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ይነገራል:: ከዛም በቀዳማዊ ኅይለሥላሴ ዩንቨርሲቲ የህክምና ትምህርት ሲከታተል ቆይቶ እስከሁለተኛ ዓመት ድረስ ዘልቋል:: እስከዚህ ጊዜ ድረስ መልካም ዘር የዘራበት ነበር ማለት ይቻላል:: መጥፎ ዘር መዝራት የጀመረው የከፍተኛ ተቋም ትምህርቱን አቋርጦ ጫካ ከገባ በኋላ ይመስላል:: የጥፋቱ መጠንና ዓይነት ዘርፈ ብዙ ስለሆነ ዘርዝሮ መጨረስ አስቸጋሪ ይሁን እንጂ አያዳግትም:: ስለሆነም አንኳር አንኳር የሆኑትን የጥፋት ዘሮች እንደሚከተለው እንዳሳቸው:: በዱርቤቱ የዘራው ለአስራ ሰባት ዓመታት ያህል ተንኮል እየቀመመ በጓዶቹ ላይ ዘመተ:: የንጹሃን ጓደኞቹን ሕይወት

The Meles Mystery: Has Anyone Seen Ethiopia’s Prime Minister Zenawi?

by Graham Peebles
To many Ethiopians the sudden disappearance of Prime Minister Zenawi is a source of joy and excited expectation, for
Meles Zenawi
his die-hard supporters apprehension no doubt and concern for their leader. Is he dead they ask, or perhaps critically ill, has he run away, finally overwhelmed by guilt and shame at the way he and his ministerial cronies have treated the people of Ethiopia, since they took power from the communist Derg twenty one years ago. Or is he recovering from illness peacefully on some isolated retreat.

መንግስት በሀይማኖት ጣልቃ መግባቱን ያቁም!

ትኩስ መረጃ
ሙስሊም ሆይ ይህን ጉድ ሰማህን፤ ላልሰማው አሰማ!!!
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒሰተር፤ የኢህአዴግ የድርጅት ጽ/ቤት እና የብሄራዊ ደህንነትኤጀንሲ የዒድን ሰላት ለማጨናገፍ ያለ የሌለ ኃይላችውን አሟጠው እየሰሩ መሆኑንየውስጥ ምንጮቻችን አስታወቁ፡፡ በጣም በሚገርም ሁኔታ ለዚህ ጉዳይ የመንግስትንመዋቅር ከመጠቀም አልፎ ሌላ ስራና ኃላፊነት የሌለባቸው እስኪመስል እያንዳንዱ የመንግሰት ቢሮ የራሱን አክሽን ፕላን አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ለዚህም የአህለሱና ወል ጀማዓሱፊያ የሚባል የአህባሽ ማ...
ህበር በመላው አ/አበባ በማቋቋም ሰላማዊ ተቃውሞዋችንንለመግታት አስበው ባሳለፍንው ሳምንት በየሰፈሩ እየዞሩ አንድ ለአምስት ተደራጁበማለት ሊከውኑት የነበረው እንቅስቃሴ ባለፈው ቅዳሜና እሁድ በሙስሊሙ የነቃ ተቃውሞ ሙሉ በሙሉ ሊከሽፍ ችሏል፡፡ ለአብነት ያክል በኮ/ቀራንዮ ክ/ከተማ ዉስጥ ባሉት 15 ወረዳዎች የኢህአዴግ የየወረዳው ካድሬዎችና በበድኑ

በኢህአዴግ ዉስጥ የተፈጠረዉ የስልጣን ሽኩቻ ተጠናክሮ ቀጥሏል

Ethio Hot blog
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በሕይወት መኖር አለመኖር አጠያያቂ በሆነበት በዚህ ሰዓት በኢህአዴግ ዉስጥ የተፈጠረዉ የስልጣን ሽኩቻ እያደገ መምጣቱንና በተለይም ሰሞኑን አፍለኛ የከተማ ካድሬዎች በበረከት ስምዖን ዙሪያ መሰባሰብ መጀመራቸዉን የኢህአፓ ድምፅ የሆነዉ ፍኖተ ህብረት የተሰኘዉ ሬድዮ ዘግቧል፡፡
በተያያዘም በዘገባዉ እንደተጠቆመዉ የኢህአዴግ የደቡብ ክንፍ የሆነዉ ደኢህዴን ከህወሓት ጋር እየወገነ ሲሆን ብአዴን ግን አሁንም በልዩነቱ ፀንቶ የዉስጥ ለዉስጥ ፍትጊያዉን አፋፍሞ ቀጥሏል፡፡
በቤተ-መንግስት አካባቢ አቶ በረከት ስምዖን እንዲሁም የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የሆኑት ዶ/ር ቴወድሮስ አድሀኖ እና የመከላካያዉ ኢታማጆር ሹም ሳሞራ የኑስ ብቻ በብዛት እንደሚታዩ የቤተ-መንግስት ምንጮችን ጠቅሶ የዘገበዉ ፍኖተ ህብረት ብዙ ሰዎች አገሪቱ በእነዚህ ሰዎች መዳፍ ስር ናት እያሉ ይገኛል ሲል አትቷል፡፡

Tuesday 14 August 2012

ESAT Ethiopian News August 14, 2012


‹‹ሆያ ሆዬ… ያች ድንክ አልጋ…ሆ… አመለኛ›› – ከተመስገን ደሳለኝ




በልጅነት ዕድሜያችን ከሚወደዱ እና ከሚናፋቁ ወራቶች ነሐሴ ዋነኛው ነው። በተለይ ለብላቴናዎች። ለወሩ ተወዳጅነት ምክንያት የሆነው ደግሞ በ‹‹ሆያ ሆዬ›› ጭፈራ የሚከበረው የ‹‹ቡሄ›› ባህል በዚህ ወር መሆኑ ነው። ስለዚህም ከወሩ የመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ‹‹ጅራፍ›› እየገመዱ በሚያስጮኹ ማቲዎች መንደሮች ይታመሳሉ። በዚህ አይነት መልኩ እየተዝናኑ ይቆዩና ዕለቱ ሲደርስ ተቧድነው ‹‹ሆያ ሆዬ›› ዕያሉ በየቤቱ ይዞራሉ።
ሆያ ሆዬ

ሆዬ የኔ ጌታ

እዛ ማዶ ሆ፣ ጭስ ይጨሳል
አጋፋሪ ይደግሳል
ያችን ድግስ ውጬ ውጬ
በድንክ አልጋ ተገልብጬ
ያች ድንክ አልጋ አመለኛ
ያለ አንድ ሰው አታስተኛ…
ክፈት በለው በሩን የጌታውን

ለሦስት ግራም ወርቅ ዐርባ ስድስት ሚሊዮን ብር?




ይሄይስ አእምሮ
ሀገራችን የጉድ መንተክተኪያ ጎላ ድስት ከሆነች ቆየች፡፡ ባለሥልጣን ከናካቴው የለንም ወይም ሁሉም በየፊናው ባለሥልጣን ሆኗል፡፡ ተጠያቂነት የሚባል ነገር ድራሹ ጠፍቷል፡፡ ነገረ ሥራችን ሁሉ የአባትህ አገር ሲወረር አብረህ ውረር ዓይነት ነው፡፡ ሁሉም ባመቸው አጋጣሚ የቻለውን መቦጨቅና ኢንቬስተር መሆን በተለይ ለወያኔያውያን በጣም የተንቦረቀቀ መስክ ከሆነ ሰነበተ፡፡ እስኪ ስለ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ትንሽ እናውራ፡፡ ከመሪያችን ሁኔታ በተጓዳኝ ይህም ነገር ሰሞነኛ ነው፡፡ ትንሽ እንቆዝም፡፡
አሠራሩ እንደማንኛውም የመንግሥት ቤት ሁሉ መደዴ እንጂ በሕግና በሥርዓት የሚመራ አይደለም፡፡ ከሞላ ጎደል በሁሉም የሀገራችን የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ሥርዓተ አልበኝነት እንደነገሠ ሁሉ በዚህ ቤትም ይሄው ችግር ጥርሱን ባገጠጠ መልኩ እንደተንሠራፋ ከዚያው አካባቢ የሚናፈሱ ወሬዎች

Monday 13 August 2012

የግፍና የሰቆቃ እስር በኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች ቀጥሏል


ከኢንጅባራው ዘላለም
ኢህአዴግ እስር ቤቶቹን “ማረሚያ ቤቶች” እያለ ቢጠራቸውም፣ መጠሪያው እውነተኛውን የእስር ቤቱን ገጽታ ስለማይገልፀው እንደ ቀድሞ ስሙ “ወህኒ ቤት” ተብሎ ቢጠራ የተሻለ ይመስለኛል፡፡ የኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች ከዚህ በፊት ከነበሩት የከፉ ናቸው ለማለት ይቻላል፡፡ ምክንያቱም የግፍና የሰቆቃ እስሩ እጅግ ሰብአዊነት በጐደለው ሁኔታ በፖለቲካ አስተሳሰብና በዘር ላይ ያነጣጠረ መሆኑ ነው፡፡ ቃሊቲ ወህኒ ቤት እስር ቤት ብቻ ሳይሆን የመረጃ ማዕከልም ነው፡፡ የመላው አገሪቱ የዕለት ተዕለት መረጃ በትኩሱ በቅብብል ይደርሳል፡፡ በመላው የኢትዮጵያ እስር ቤቶች ያለው ሁኔታም በየዕለቱ ይሰማል፡፡
ባለፈው ጽሁፌ ራሴን ለማስተዋወቅ እንደሞከርኩት በዚህ የዘረኞች ወህኒ ቤት 19 ዓመት ከ8 ወር ቆይቼአለሁ፡፡ እኔ ከዚህ ሳልወጣ አራትና አምስት ጊዜ ተመላልሶ የታሰረ እስረኛ አጋጥሞኛል፡፡ የሸዋሮቢት፣ የዝዋይና በቅርቡ ሥራውን የጀመረው የቂሊንጦ ከፍተኛ ወህኒ ቤት በመረጃ ደረጃ የሁለት የጐረቤታሞች ያህል መረጃ እንለዋወጣለን፡፡ በዚሁ መሠረት ዛሬ ህዝብ ስለማያውቃቸው ድብቅ እስር ቤቶችና በየድብቅ እስር ቤቶቹ ስለሚፈፀሙ ግፈኛ ድርጊቶች ላውጋችሁ፡፡ ወያኔ/ኢህአዴግ “በአገሪቱ ውስጥ የፖለቲካና የህሊና እስረኛ የለም” ይለናል፡፡ ምንም እንኳን መኖሪያ
ቤታችን ቃሊቲ ቢሆንም የመንግስትን መረጃ በተሟላ ሁኔታ እንከታተላለን፡፡ ሬዲዮ ከተከለከልን ሦስት ዓመት ቢልፈንም፣ በቃሊቲ ኢቴቪ 24 ሰዓት ይሰራል፡፡ የውጭ ሚዲያዎች የሚያወሩትን ውጭ ካለው በበለጠ እንሰማለን፡፡

የተሰሩት የአ.አ ሕንጻዎች ለአካል ጉዳተኞች ግልጋሎት ምቹ አይደሉም ተባለ Ethiopia News

(ዘ-ሐበሻ) የወያኔ ጀነራሎች፣ የጊዜው ባለስልጣናትና የባልስጣናት ዘመዶች የገነቧቸው ሕንጻዎች (ከወያኔ ጋር ያልተወዳጀ ሕንጻ አይደለም ራሱ ሃገር ውስጥ እንዲኖርለት አይፈቀድም) በአዲስ አበባ የገነቧቸው ግዙፍ ሕንጻዎች ምንም እንኳ በርከት ያሉ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የተመዘበሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ገንዘቦች ቢፈሱባዎቸውም ህንጻዎቹ ግን የተገነቡት አካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ባዳረገ መልኩ አለመገንባታቸውን የወያኔ ሚዲያዎች ራሱ አመኑ።
ራድዮ ፋና የተባለው የካድሬዎች የመፈልፈያ ራድዮ ዛሬ ባስተላለፈውና የአካል ጉዳተኞችን እያነጋገረ ባቀረበው ዘገባው በአዲስ አበባ ከሚገነቡ አብዛኛዎቹ ህንጻዎች ለአካል ጉዳተኞች የተመቸ መወጣጫ እንደሌላቸው ፥ የአሳንስሮችም ተሽከርካሪ ወንበር ፣ ዊልቸሮችን ማስተናገድ የማይችሉ ናቸው መሆናቸውን አስተያየት ሰጪዎቹ ተናግረዋል።
የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የህንጻ አዋጅና ደንብ በ2001 ዓ.ም ማንኛውም የሚገነባ ሕንጻ የአካል ጉዳተኞችን ታሳቢ ማድረግ እንዳለበት ቢደነግግም ላወጡት ሕግ ቀርቶ ለራሳቸው የስነምግባር ሕግ የሌላቸው የወያኔ ባለስልጣናት ይህን ሕግ ጥሰዋል። መስሪያ ቤቱ ከአሁን በኋላ ለሚሰሩ ሕንጻዎች አስገድዳለሁ ቢልም እስካሁን ለተሰሩ ሕንጻዎች ግን

ESAT Daily News, Washington D.C. August 13 (the latest)


መነገር ያለበት ቁጥር ሁለት! በልጅግ ዓሊ

አብደላ ኦጀላን(Abdullah Ocalan) የኩርዲስታን የሠራተኛ ፓርቲ (Kurdistan Workers’ Party) መሪ ነበር። ይህ ግለሰብ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1999 ኬንያ ውስጥ ተይዞ ዓይኑ በእራፊ ጨርቅ ተሸፍኖ፣ ሁለት እጆቹ ታስረው ወደ ቱርክ ሲወሰድ በዓለም የዜና ማሰራጫ በወቅቱ ታይቷል። በአሁኑ ወቅት አብደላ በቱርክ መንግሥት የዕድሜ ልክ ፍርድ ተበይኖበት ለብቻው በአንድ ደሴት ላይ ታስሮ ይገኛል።
አብደላ ከመታሰሩ በፊት ድርጅቱን የሚመራው ከኩርድ ሕዝብና ጦር ተለይቶ ሶርያ ውሰጥ ሆኖ ነበር። የኩርዶች ትግል በጠነከረ ወቅት የቱርክ መንግሥት፣ ሲ.አይ. ኤና ሞሳድ በመተባበር ይህንን ድርጅት ለማጥፋት ይታገሉ ጀመር። በሶርያ መንግሥት ላይ ባደረጉት ተጽዕኖ ከሶርያ እንዲወጣ ተደረገ። የቱርክ ጠላት ነች የምትባለውም ግሪክ አልቀበልም አለች። መጨረሻ ኬንያ ሃገር እንዲሄድ ተደርጎ በቱርክ የደህንነት ድርጅት አባሎች ተይዞ ቱርክ ውስጥ ታሰረ። በዚያ ወቅት የሚከላከልለት ጦር፣ የሚደብቀው ሕዝብ አላገኘም። አንድ መሪ ከሚመራው ሕዝብ ከተለየ ከባሕሩ የወጣ ዓሣ ነው የሚሆነው። ከምትመራው ሕዝብ ተነጠለህ የሌላ ሃገር ጥገኝነትን አምነህ መሄድ የሚፈጥረው ችግር አንዱ ይህ ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ጥገኝነት የጠየከውን መንግሥት ጥቅም እንድታስጠብቅ ትገደዳለህ። ከዚህ ሁሉ ተጽዕኖ ነጻ ለመውጣት አማራጩ ከሕዝብ ውስጥ መገኘት ነው። የምትመራው ሕዝብ ከወደደህ ይደብቅሃል። የምትመራው ሕዝብ ከጠላህ ያጋልጥሃል። ከዛስ አልፎ ከሕዝብህስ ጎን ሆነህ ብትሰዋ ከዛ የበለጠ ታላቅነት ምን አለና ነው?

Mystery of Ethiopia’s missing dictator

The Independent
Ethiopia’s missing prime minister has been taking part in diplomatic efforts to resolve the Sudan crisis from his sick bed,
Meles Zenawi
according to African Union officials.
Meles Zenawi, Ethiopia’s normally highly visible premier, has not been seen in public since June, and his government has refused to release any details of his condition.
His disappearance saw opposition groups claim that the 57-year-old had died, while there are unconfirmed reports that he has been treated for a brain tumour.
His absence became more apparent as Ethiopia hosted an important African Union summit in the capital, Addis Ababa, where Mr Meles would have expected to lead efforts to defuse the crisis in DR Congo and the simmering dispute between Sudan and newly independent South Sudan.

ESAT News Weekly August 12 (the latest)

ESAT is the first independent Ethiopian Satellite Television service and Radio Station who broadcast to Ethiopia and the rest of the world

Sunday 12 August 2012

የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንደሆነ ተገለጸ

የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የጤና ሁኔታ ለሕዝብ በግልጽ ባልተገለጸበት በዚህ ወቅት፤የሀገሪቱ መከላከያ ሰራዊት በከፍተኛ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን ትእዛዝ መሰጠቱንና፤ ላለፉት ሶስት ቀናት ተግባራዊ ሆኖ መቀጠሉን የመከላከያ ምንጮች ገለጹ።
መንግስት የመከላከያ ሰራዊቱ በአንደኛ ደረጃ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆን ትእዛዝ የሰጠው ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ መሆኑ ለሰራዊቱ ተገልጿል።
ይሁን እንጂ፤ ወታደራዊ ባለሙያዎችና አንዳንድ የመከላከያ ምንጮች፤ ማስጠንቀቂያው ከሙስሊሞች እንቅስቃሴ ይልቅ፤ ከአቶ መለስ ጤና ሁኔታ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ግምት ሰንዝረዋል::
በዚህ ሳምንት የኢትዮጵያ ምድርና የአይር ሀይል አባላት፤ በአንደኛ ደረጃ ተጠንቀቅ ላይ እንዲሆኑ ከመከላከያ ሚኒስቴር በወረደ ትእዛዝ መሰረት፤ በአዲስ አበባ ከተማና በደብረዘይት አየር ሀይል ግቢ፤ ሰራዊቱ ከመደበኛ የስራ ሰዓት ውጭ በስራ ገበታው በተጠንቀቅ ሆኖ ተግባሩን እንዲቀጥል መታዘዙ ታውቋል።

Ethiopian Democratic Political and Civic Groups Embrace a Common position and Call for Unified Action Joint Statement


 
 
 

We, the undersigned believe that, the dictatorial single party rule of the minority ethnic-based Tigray People’s Liberation Front (TPLF) and the Ethiopian Peoples’ Revolutionary Democratic Front (EPRDF) it dominates, faces the prospect of sustained popular resistance and inevitable demise that its oppressive predecessors also faced. The Ethiopian people and the world community continue to watch an unfolding drama with anxiety and uneasiness emanating from the widely reported “critical illness” and disappearance of Prime Minister Meles Zenawi, the face of the governing party for the past 21 years. Ethiopian society is replete with gossips, rumors, widespread speculation concerning the closely guarded meetings and rivalry within the governing party, for succession. This occurs in an environment of fear, repression of all forms of dissent, gross human rights violations, hyperinflation, high unemployment and

Ethiopian authorities crack down on Muslim press

CPJ
Nairobi, August 9, 2012–Ethiopian authorities must release a journalist who has been detained for almost three weeks, and allow three Muslim news outlets to resume publishing immediately, the Committee to Protect Journalists said today. Local journalists believe the Muslim press in Ethiopia is being targeted for its coverage of protests by the Muslim community.
In recent months, Ethiopian Muslims have begun staging protests on Fridays to oppose government policies they say are interfering with their religious affairs, according to news reports. These protests are a highly sensitive issue for the government, which fears a hardline Islamist influence within the predominantly Christian country, news reports said. Local journalists believe the recent harassment of Muslim journalists and newspapers are part of an attempt by Ethiopian authorities to quell coverage of the ongoing protests in the capital.
At least eight police officers raided the home of Yusuf Getachew, editor of YeMuslimoch Guday (Muslim Affairs), in the evening of July 20 in the capital, Addis Ababa, and took the journalist to the Maekelawi Federal Detention Center, according to local journalists. The police also confiscated four of Yusuf’s mobile phones, his wife’s digital camera, books, and 6,000 birr (US$334), the same sources said.

አብዮታዊ-ዴሞክራሲ-ልጆቿን-እየበላች-ነው


 ከአቤ ቶኪቻው
ይህ ጨዋታ ለዚህ ሳምንት ፍትህ ጋዜጣ የተላከ ነበር። ነገር ግን ፍትህ አሁንም በሀገሪቱ እንድትኖር ሰዎቻችን አልፈቀዱም። በፍርድ ቤት የታዘዘው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት “መጀመሪያ ሌላ ቦታ አሳትሙና በሚቀጥለው ሳምንት እኔ አትምላችኋለው” ብሎ መልስ ሰጠ ሲባል ሰማሁኝ። ይሄ በጣም አስቂኝ ነው…! ሌላ ማተሚያ ቤት እኮ የለም። አንድ ቦሌ ማተሚያ ቤት ነበረ እርሱም ደንበኛችን ስላልሆናችሁ አናትምላችሁም ብሏል። ወደየት እየተገፋን እንደሆነ እግዜር ይወቀው! እስቲ ለማንኛውም ወጋችን ይጀምር… ሰላም ወዳጄ እንዴት ሰነበቱልኝ? ፍትህ ጋዜጣ በፍትህ ችግር ታግታ ሰነበተችና ተጠፋፋን አይደል!? ጉልቤው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ያለ ምንም ህጋዊ አግባብ የእናንተን ጋዜጣ አላትምም ብሎ ደጅ ሲያስጠናን ቆይቶ ይኸው ዛሬ “የተከበረው” ፍርድ ተቆጥቶልን ለመገናኘት በቅተናል። ብዬ ነበር የጀመርኩት… እኔማ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማክበር የሁላችንም ግዴታ መስሎኝ ነበር። ለካስ ፍርድ ቤቱን ማክበር የአንዳንዶቻችን ብቻ ነው…! አንድ ቀን አንዳንድ ከመሆን ተላቀን አንድ እንሆን ይሆናል! ብቻ ግን አስቲ ወጋችን ይቀጥል… ፍርድ ቤት ካልኩኝ አይቀር፤ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላትን “ክቡር” ፍርድ ቤቱ “ኑ እንመካከር” ብሎ ጠርቷቸው ሲያበቃ ምንም ባልተከሰሱበት እና ባልተከራከሩበት ችሎት ገትሮ