No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Wednesday 10 October 2012

መምህሩም ያስተምር ተማሪውም ይማር

የተማረ ሆኖ ዕውቀቱን የማይገልጽ፣
ባለፀጋ ሆኖ ገንዘቡን የማይሰጥ፣
ደሃ ሆኖ መሥራት የማይሻ ልቡ፣
ሶስቱም ፍሬ ቢሶች፣
ለማንም አይረቡ።
Kids in school, Ethiopiaታዋቂው ደራሲ ከበደ ሚካኤል ይህንን ብለውን አልፈዋል። ደራሲው ዕድሜ ለግሷቸው መምህሩም ለማስተማር ተማሪውም ለመማር አለመቻላቸውን ዛሬ ቢያዩ ምን ይሉ? በሃያ አንደኛው መቶ ዓመት ጉግ ማንጉጎች ተፈጥረው የዕውቀት ጮራ በሃገራችን ምድር እንዳይፈነጥቅ ጋርደዋት በጭለማ ውስጥ ትገኛለች።
‘እንዳያማህ ጥራው እንደይበላ ግፋው’ እንደሚባለው በአለፉት ሃያ ዓመታት ዩኒቭርሲቲዎች ተከፈቱ ቢባልም፤ የተማሪዎቹ ቁጥር ቢጨምርም፤ ተቋማቱ የመማርና የማስተማር ሥራ የሚካሄድባቸው ሥፍራዎች ሆነው አልተገኙም። የአካዳሚ ነፃነት በሌለበት በዕውቀት እድገት የለም። ተቋሞቹ የዕውቀት መገብያ ሳይሆኑ የካድሬ መፈልፈያ የስለላ ሥራ ማካሄጃ ናቸው። ይህም ሁኔታ በነፃነት መምህሩም ለማስተማር ተማሪውም ለመማር

Tuesday 9 October 2012

ESAT Daliy News-Amsterdam Oct. 09 2012 Ethiopia


የኤርፖርቶች ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚና ሰባት ኃላፊዎች ከአገር እንዳይወጡ ታገዱ

-    ቃላቸውን ሰጥተው በ10 ሺሕ ብር ዋስ ተለቀዋል
-    በተርሚናል ውስጥ ያሉ ሱቆች ጨረታ ጊዜ ማለፉ እያነጋገረ ነው

በታምሩ ጽጌ
ከዓመታት በፊት ወጥቶ ከነበረ ጨረታ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ዓለሙና ሌሎች ሰባት የድርጅቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች ከአገር እንዳይወጡ መታገዳቸውን ምንጮች ገለጹ፡፡ ኃላፊዎቹ ከአገር እንዳይወጡ የታገዱት የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ለደኅንነት፣ ኢሚግሬሽንና ስደተኞች ባለሥልጣን የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ ዋና መምርያ መስከረም 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ደብዳቤ በመጻፉ ነው፡፡ መምርያው ደግሞ ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ መስከረም 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሠረት መታገዳቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል

Sunday 7 October 2012

የ21ኛው ክፍለ ዘመን ይሁዲ (ከማተቤ መለሰ ተሰማ)

በ20ኛው ክፍለ ዘመን የአርያንን ዘር በዓለም ላይ ማንገስን ሰነቆ የተነሳው የጀርመኑ ናዚ፡ በይሁዲያዊያን ላይ የፈጸመው የዘር ማጥፋት ሰቆቃ ዛሪ ድረስ የዓለምን ህዝብ ሲያሳዝን ይገኛል። አሁን በ21ኛው ክፍለዘመን ደግሞ ወያኔ የአማረኛ ቋንቋ ተናጋሪና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ተከታይ የሆነውን ኢትዮጵያውያን ከምድረገጽ ለማስወገድ እንደ ያኔው ናዚ ዘግናኝ ድርጊት በመፈጸም ላይ ነው።
ይህ የጥፋት ዘመቻ በአጋጣሚ የተከሰተ ሳይሆን በእቅድ ተነድፎ እየተከናወነ ያለ መሆኑን የህዋሀቱ አንጋፋ ታጋይ አቶ ስብሃት ነጋ የአቶ ሐይለማርያም ደሳለኝን የኢስሙላ ጠቅላይ ሚኒስተርነት ሹመት አስመልክቶ ገዛ ተጋሩ ከተባለ ፓለቶክ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፡ ስልጣንን ከኦርቶዶክስ እምነት ተከታይና ከአማራ ነጥቀነዋል አላማችንም የኸው ነበር ሲሉ ሰነምግባር ባልገራው