የተማረ ሆኖ ዕውቀቱን የማይገልጽ፣
ባለፀጋ ሆኖ ገንዘቡን የማይሰጥ፣
ደሃ ሆኖ መሥራት የማይሻ ልቡ፣
ሶስቱም ፍሬ ቢሶች፣
ለማንም አይረቡ።

‘እንዳያማህ ጥራው እንደይበላ ግፋው’ እንደሚባለው በአለፉት ሃያ ዓመታት ዩኒቭርሲቲዎች ተከፈቱ ቢባልም፤ የተማሪዎቹ ቁጥር ቢጨምርም፤ ተቋማቱ የመማርና የማስተማር ሥራ የሚካሄድባቸው ሥፍራዎች ሆነው አልተገኙም። የአካዳሚ ነፃነት በሌለበት በዕውቀት እድገት የለም። ተቋሞቹ የዕውቀት መገብያ ሳይሆኑ የካድሬ መፈልፈያ የስለላ ሥራ ማካሄጃ ናቸው። ይህም ሁኔታ በነፃነት መምህሩም ለማስተማር ተማሪውም ለመማር