No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Friday 14 December 2012

አንድነት ስየን ሊሰርዝ ወይም ሊያስጠነቅቅ ይችላል የተሃድሶው ጅማሬ ይሆን?

በነባር አመራሮች ሲንከባለል የኖረው “የቅንጅት ወራሽ” አንድነት ፓርቲ ኃላፊነቱንና አመራሩን ለተተኪ ሳያስረክብ መቆየቱ በአብዛኛው ትችት ሲያሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተለይም አቶ ስየ አብርሃ ፓርቲውን በተቀላቀሉ ማግስት በከፍተኛ ኃላፊነት መሰየማቸው አልተወደደለትም ነበር፡፡ በአንድነት ፓርቲ ውስጥም እስከመከፋፈል የዘለቀ ልዩነት መፍጠሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡
አሁን የረገበ የሚመስለው የፓርቲው የውስጥ ልዩነት፤ በወቅቱ “ዝም አንልም፤ መርህ ይከበር” የሚሉት ኃይሎች የወሰዷቸውን ጽንፈኛ አቋሞች ብዙዎች የሚደግፉት ባይሆኑም ያነሱትን ጥያቄ አግባብነት ግን ይቀበላሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊመንበር የነበሩት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም “እኛ የማማከር አገልግሎት መስጠት አለብን፤ አመራሩን መያዝ ያለበት አዲሱ ትውልድ ነው” በማለት ራሳቸውን በቅሬታ ከፓርቲው ማግለላቸው ይታወሳል፡፡

Tuesday 11 December 2012

ESAT Daliy News-Amsterdam Dec. 11 2012 Ethiopia


በ2012ቱ ዓለም አቀፍ የአገሮች የሙስና ሰንጠረዥ፤ የኢትዮጵያ ገጽታ በጨረፍታ


«ሙስና በከፋባቸው አገሮች የሰብዓዊ መብት አያያዝም ያንኑ ያህል የከፋውን መስመር ይይዛል፤» ሲሉ የ2012ቱን ዓመታዊ የአሮች ገጽታ በመግቢያቸው የቃኙት ካናዳዊቷ የድርጅቱ ሊቀመንበር Labelle ናቸው።
ከሰሃራ በስተደቡብ ከሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ትልቋ የዩናይትድ ስቴትስ እርዳታ ተቀባይ የሆነችው ኢትዮጵያ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የሲቪል ማኅበረሰብ ይዞታዋ እየተዳከመ መምጣቱን የሚናገሩ ተችዎቿ፥ “በጸረ-ሙስና ዘመቻውም ክፉኛ ወድቃለች፤ ይላሉ። ለዚህም አንዱ ምክኒያት፤ የሙስናው ተዋናዮች በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የመንግስት ባለሥልጣናት ጭምር መሆናቸው ነው፤” ሲሉ ይወነጅላሉ።
ኢትዮጵያ የህዝቧን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል በእጅጉ ስትጥር መቆየቷን ያመለከቱት  Labelle ባለፉት ጥቂት ዓመታት የሚታየው ግን አሳሳቢ ሁኔታዎች ጎልተው መታየት መቀጠላቸውን አመልክተው፤ “ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሲቪል ማኅበረሰቦች ያላቸው ሥፍራ እየጠበበ መምጣቱ አንዳንድ አሳሳቢ ሁኔታዎችን ከስቷል። ያ ጤናማ አይደለም። ጥሩም አይደለም። መንግስት ያ አቀራረብ ለኅዝቡም ሆነ