No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Sunday 2 February 2014

የድንጋይ ዉርወራ ፖለቲካ በዓዲግራት by Abraha Desta


ዓረና-መድረክ ለጥር 18, 2006 ዓም በዓዲግራት ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ ይታወሳል። ዓዲግራት ከተማ ከመቐለ በስተሰሜን በኩል በ120 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች። የስብሰባው ዓላማ ከዚህ ቀደም በዉቅሮ፣ ማይጨው፣ ዓብይ ዓዲና ሽረ ከተሞች እንዳደረግነው ሁሉ የዓረና ፓርቲ ዓላማዎችና ፖሊሲዎች ከህዝብ ጋር ለማስተዋወቅ እንዲሁም ህዝብን ፖለቲካ ማስተማርና ማደራጀት ነበር።

ስብሰባ ለማካሄድ ተፈቀደልን። የማዘጋጃቤት አዳራሽም ተሰጠን። ስብሰባ ለማድረግ ማስፈቀድና አዳራሽ ማግኘት በቂ አልነበረም። ህዝብ በስብሰባው እንዲሳተፍ የጥሪ ወረቀት መበተን ነበረብን። በማይክሮፎንም ማወጅ ነበረብን። ዓረና በዓዲግራት ከተማ ስብሰባ መጥራቱ ለማብሰር የዓረና ፓርቲ ልኡክ ወደ ዓዲግራት ከተማ ሐሙስ ጥር 15, 2006 ዓም ተላከ።

ዓርብ ጥር 16, 2006 ዓም ጧት የልኡካን ቡድኑ ለሁለት ተከፍለው ዓዲግራት አቅራቢያ በሚገኙ የዕዳጋ ሐሙስና የፋፂ ከተሞች የስብሰባው ቅስቀሳ አደረጉ። ወደ ፋፂ የተላከው ቡድን የተሳካ ቅስቀሳ አድርጎ በሰላም ወደ ዓዲግራት ሲመለስ በዕዳጋ ሐሙስ የነበረ ቡድን ግን “ሕጋዊ አይደላችሁም” በሚል ሰበብ የዓረና ፓርቲ የህዝብ ግንኙት ሐላፊ የሆነው አቶ ዓምዶም ገብረስላሴና መምህር ሃይለ ገብረፃዲቅ ታሰሩ። ከሰዓታት እስር በኋላ ተፈቱ። ወደ ዓዲግራትም ተመለሱ።

በጎንደር መስቀል አደባባይ በከፍተኛ ድምቀት ሲካሄድ ያረፈደው ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠናቋል።

February 2, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ባደረጉት የመዝጊያ ንግግር የተፈጸመው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ፣ በአይነቱ በጎንደር ያልተለመደ ነው።
ሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር ህዝብን አስተባብሮ ባደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ወያኔ በሚስጥር ከሱዳን መንግስት ጋር ተደራድሮ መሬት ለሱዳን አሳልፎ መስጠቱንና ወደፊትም ተጨማሪ መሬት ለመስጠት በመዘጋጀት ላይ መሆኑን የጎንደር ህዝብ ግንዛቤ እንዲኖረው አድርጓል።