No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Saturday 23 February 2013

መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

በአለፉት ሠላሳ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ችግሮችን መፈልፈያ መሣሪያ ሆናለች፤ ለብዙ ምዕተ-ዓመታት ይዘናቸው (ምናልባትም አቅፈናቸው ማለት ይሻል ይሆናል) ስንንከባለል የቆዩ ችግሮች ሞልተውናል፤ እያሰብን እነዚያን የቆዩ ችግሮቻችንን በመፍታት ፋንታ ሌሎች አዳዲስ ችግሮችን እየፈለፈልን የተቆላለፉና የተወሳሰቡ፣ ውላቸው የጠፋ ችግሮችን ፈጥረናል፤ እየፈጠርንም ነው፤ አሁን በመፈጠር ላይ ያለው አዲስ ችግር እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ የሚል ነው፤ እስቲ እንመልከተው፡፡

በሩቁ እንጀምር፤ እስላማዊ መንግሥታት ያቋቋሙ አገሮች አሉ፤ አንዳቸውም ሰላም የላቸውም፤ እስላማዊ ቡድኖች በምርጫ አሸንፈው ሥልጣን የያዙ አሉ፤ ለምሳሌ በቅርቡ በአረብ አገሮች በተጀመረው የፖሊቲካ እድገት ለውጥ በቱኒስያና በግብጽ እስላማዊ ቡድኖች

Kenya Presidential Debate 2013 [Full Video]


Friday 22 February 2013

ሰበር ዜና – አስመራጭ ኮሚቴው ለዕጩነት የለያቸው አምስት ሊቃነ ጳጳሳት ታወቁ !!

ሐራ ዘተዋሕዶ
  • ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል እና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል አልተካተቱም
  • ሁሉም የኮሚቴው አባላት በውሳኔው ስለመስማማታቸው አጠራጣሪ ኾኗል
  • የፓትርያሪክነት መመዘኛ መስፈርቱ ከዕጩዎች ማንነት ጋራ በአግባቡ ይረጋገጥ
  • ‹‹ዕጩዎቹን ስታውቅ ፓትርያሪኩን ታውቃቸዋለኽ››› /ሰሞንኛ አባባል/
የስድስተኛው ፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ ለዕጩ ፓትርያሪክነት አጣርቶ የለያቸውን አምስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ለቋሚ ቅ/ሲኖዶሱ ማቅረቡ ተሰማ፡፡ ከየካቲት ዘጠኝ ቀን ጀምሮ የዕጩዎች ልየታ ሲያካሂድ የቆየው አስመራጭ ኮሚቴው÷ ለፓትርያሪክነት ለመመረጥ ብቁ ናቸው ብሎ ያመነባቸው የአምስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ስም ዝርዝር፡-

Crimes in the name of the people of Tigray

There is no telling why Woyane have choice to tarnish good will of Tigray and associate it with crime of atrocity and corruption. Whatever the reason may be, it is part of the grad plan of tearing Ethiopians apart. The desperate regime and its vulgar henchmen don’t seem to understand the day of making drama to prolong Woyane rule is coming to end. 

Wednesday 20 February 2013

የታማኝ ጥሪ ለተቃዋሚ ኃይል መሪዎች – ታማኝነት ያፈራውን ህዝባዊ ፍቅር ተረከቡኝ ነው



“ህዝቡ መሪዎችን ተጣራ! … ሳትሰሙ ብትቀሩ ግን ግፍ ይሆናል! … እኔ ተራው ሰው ይህንን የህዝብ ጥያቄ የመሸከም አቅሙም ብቃቱም የለኝም! የመነጋገሪያና የመደማመጫ ጊዜያችሁ አሁን ነው! እባካችሁን?!” በማለት የተቃዋሚ ኃይሎችን እንደ ድርጅት የህዝብን ፍላጎት እንዲረከቡና እንዲመሩ ከሰበዕዊ መብት ተሟጋቹ ከአርቲስት ታማኝ በዬነ ጋር በተደረገው ቃለ ምልለስ ከኢሳት Feb 18, 2013 ከዕለታዊ ዜና ጋር አዛምዶ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ካቀረበው የተወሰደ።
“ህዝብ መሪዎችን ተጣራ!” መንገድ ጠራጊው ለአዲስ ምዕራፍ – ብሄራዊ የፍቅር ጥሪ አቀረበ!

Bottom feeders of tyranny: Lazy journalist and propaganda Medias

When we Ethiopians treat adult journalists that act as toddlers in a dipper it isn’t their fault but, ours. The havoc they cause on society in the service of tyranny is because we treat them as an adult; it is inexcusable. Expecting toddlers with crayon to keep the house clean is like expecting tyranny not to lie; it is complete madness.
by Teshome Debalke
The conventional wisdom-Woyane dictatorship is the worst thing that happened to the people of Ethiopia isn’t true. It is the bottom feeders; opportunists, double thinkers and the willing ignorant that sustain Woyane that are worst. They are the natural habitat of tyranny; obstructing the struggle to end brutal and corrupt rule.

Tuesday 19 February 2013

ሞትን በሕይወት፣ ጥላቻን በፍቅር የረታ ‹‹ይቅርታ!›› ከዕንቁ መጽሔት የተወሰደ – ጸሐፊው በፍቅር ለይኩን፡፡


በደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ከተማ የሚገኙ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፣ ጓደኞቿና የነፃነት ትግሉ አጋሮቿም፡- ‹‹እናዝናለን ኤሚ…ፍቅርሽ፣ ርኅራኄሽ፣ ለሰው ልጆች ነፃነትና መብት መከበር ያለሽ ጽኑ አቋም በልባችን ለዘላለም ይኖራል፡፡ ትግላችን እንዳቺ ያሉ የእውነት፣ የፍትሕ ጠበቃዎችንና ሐቀኞችን በአጥፍ ጨምሮ ይቀጥላል…፡፡ ኤሚ እንወድሻለን፣ ሁሌም እናስታውስሻለን! አንቺ የዘረኞችን የመለያየት ግንብ የናድሽ ጀግናችን ነሽ፣ አንቺ በልባችን ውስጥ ለዘላለም ሕያው ነሽ…ሞት በአንቺ ላይ ስልጣን የለውም፣ ሞትን በሕይወት፣ ጥላቻን በፍቅር ያሸነፈሽ የሕዝባችን ታላቅ ሰማዕት ነሽና …ደህና ሁኚ ኤሚ ደህና ሁኚ፣ ሁሌም እንወድሻለን…!›› በማለት ወደ ትውልድ አገሯ አሜሪካ በእንባና በመሪር ሐዘን ሸኟት፣ ተሰናበቷት፡፡

Monday 18 February 2013

ስለ አሕበሽ በጥቂቱ:-

1. ከካፊር ጋር ቁማር መጫወት፣ የካፊርን (ክርስቲያን) ጎረቤትመስረቅና ማጭበርበር ይቻላል ብሎ
ያስተምራል።ዋናው እንዳይነቃ በድብቅ ማድረግና ዋናው መጠንቀቅ ነው ብሎ ያስተምራል፡፡ (መጽሐፉ
ሰሪህ አል-በያን፣ገጽ 133)
2. ሰሀቦችን ይሳደባል፡፡ አንዳንዶቹን ሰሀቦች ካፊር ናቸው የጀሀነም ናቸው ብሎ ጽፏል፡፡ ለምሳሌ ታላቁን የነብዩ
(ሶ.ዐ.ወ) ሆሃባ ሙአዊያ ኢብኑ አቢሱፍያን ካፊር የጀሀነም ሲልገልጿል፡፡ የነብያችን (ሶ.ዐ.ወ) ባለቤት
አዒሻን ተሳድቧል፡፡
3. በነጃሳ መስገድ ይፈቀዳል ይላል፡፡ (መጽሐፉ ቡግየቱ ጧሊብ፣ገጽ 99-100)
4. ዘካ የለም ይላል፡፡ ዘካ ከእስልምና ማዕዘናት አንዱ ነው፡፡ አህባሾች ግን ሰው ዘካ እንዳያወጣ ከወረቀቱ ብር
(ኖት) ላይ ዘካ የለበትም ይላሉ፡፡ ይህ ማለት በባንክም ይሁን በቤትዎ ቢሊዮን ብር እንኳ ካለዎ ዘካ አይስጡ
ብሎ ይቀሰቅሳሉ፡፡

የዋሾ መንግስት ጩኸት፣ ውሸት! ውሸት! ውሸት! ሉሉ ከበደ


ሰሞኑን ወያኔ የተለመደ የውሸት ድራማ ሰርቶ፤ ሲሞን በረከት በሚባል፤ የማያምር፤ የማያፍር የኤርትራ ሰው፤ ጭራሹን አማራ ነኝ ብሎ እንዲያታልል ወያኔ የቀጠረው ባእድ የፕሮፓጋንዳ ሚኒስቴር፤ የሀሰት ፊልም ደራሲና የበላይ አዘጋጅ የሆነ ሰው፤ ሰርቶ ጨርሶ ያሳለፈውን “ጂሀዳዊ ሀረካት” በሚል ርእስ ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት ከሚያደርገው ነገር የተለየ ባይሆንም፤ ቀጣይ የማናደድ ስራቸውን ለኢትዮጵያ ህዝብ አቅርበው ነበር። እንደድሮው አረፍተነገርና የስእል እንቅስቃሴ እየበጣጠሱ፤ ቆርጠው እየቀጣጠሉ፡ እየገጣጠሙ፤ ውሸት እየደራረቱ፤ ለራሳቸው ያሳምናል ብለው እንደመሰላቸው ለኢትዮጵያ ህዝብም ይመስለዋል ብለው በታመመ አእምሮ ስለሚያስቡ ለቀውታል።

ከኢትዮጵያዊው ሙስሊም የመብት ጥያቄ ጋር እንዲሁም ባህሪ ጋር ከቶም ከቶ የማይገናኝ፤ የንጹሀን ሙስሊም ወንድሞቻችንን ስም ለማጥፋት፤ መልካሙን የኢትዮጵያ ሙስሊም ሀይማኖትና ወደር የለሽ መልካም ስነምግባር ጥላሸት ለመቀባት፡ ይህንን ውብ መልኩን ለማጠልሸት፤ ብሎም ከኢትዮጵያዊ ክርስቲያን ወንድሙ ጋር ለማጋጨት ደም ለማቃባት፤(የማይቻል መሆኑን ቢያውቁትም) የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ነዝተዋል።

የኢትዮጵያ ትምህርት ፖሊሲና ችግሮቹ የኢትዮጵያ ትምህርት ፖሊሲና ችግሮቹ


ወያኔ በ21 ዓመት ቆይታው በትምህርት ፖሊሲው ላይ ይዞት የመጣው የኣንድ ቢሔር ብቻ የመጥቀም ኣላማውን ከግብ ለማድረስ በ1984ዓ ም ኣዲስ የትምህርት ፓሊሲ ቀርፆ 10ዓመት ባልሞላ ውስጥ ሶስት ጊዜ የመማሪያ መጽሐፍትን በመቀያየር ትምህርትን ከግዜ ወደ ግዜ ጥራቱ በማሽቆልቆል ዕነሆ ዛሬ ሞገደኛና በራሱ የማይተማመን ትውልድ ሊፈራ ችሏል። የወያኔን የትምህርት ፖሊሲ በተለያየ ጊዜ ያገባኛል የሚሉ መምህራን፤ተማሪዎችና ወላጆች የትምህርት ፖሊሲዎ ያለበትን ችግርና ያመጣዎን ኣሉታዎ ተግባር በተደገፈ መረጃ ቢያቀርቡም ወያኔ በማንኣለብኝነት ጥያቄዎን ለኣነሱ ሀገር ወዳድ ሙህራን ምላሹ ዕስራት፤ሞትና ስደት ገጥሟቸዋል።

“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል” ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል


/ዜና ጎልጉል/ ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት “የአስተዋይነት” ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል።
ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል።