No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Thursday 14 March 2013

ሁጎ ቻቬዝ ሚሊኖችን “ያላቀሱ” የዘመኑ ታላቅ መሪ በታምሩ ገዳ

ቬንዙዌላዊያን የመሪያችውን መሞት እንድሰሙ ሲላቀሱ


ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ የዜና እረፍታቸው ለህዝባቸው  እና ለመላው  አለም ይፋ የተደረገው  የቬንዙዌላው  ፕሬዜዳንት  ሁጎ ቻቬዝ  በብዙዎች ዘንድ አስገራሚ  እና  አወዛጋቢ  ባህሪ የተላበሱ መሪ ነበሩ፡፡ያቺ በላቲን አሜሪካ ውስጥ በተፈጥሮ ጋዝ ሃብቷ  ቀዳሚ ስፍራ  ያላት  ቬንቩዌላን ላለፉት 14 አመታት  በሶሻሊስታዊ ርእዮት  አለም አካሄድ  የመሯት  ቻቬዝ  ላለፉት  ሁለት  አመታት  ከካንሰር ህመም ጋር  ውጊያ ቢያደርጉም    በተወለዱ  በ58 አመታቸው  የሚወዱት ህዝባቸውን እና  ከበዙዎች አይምሮ  የማይጠፉ አሰገራሚ ትዝታዎቻቸውን  ጥለው  ወደ ማይቀረው አለም ሄደዋል፡፡
ቻቬዝ በህይወት ዘመናቸው  ኑሯቸውን የቀየሩላቸው  በብዙ ሚሊዮኖች   የሚቆጠሩ ቬንዙዊላዊያን  ባለፈው አርብ እለት  በተካሄደው  የአስክሬን  ስንብት  ስነ ስርአት  ላይ በመገኘት  ለታላቁ መሪያቸው  ያላቸውን ዘለአለማዊ ክብር እና ፍቅር  ለመገለጽ አብዛኞቹ ከ26 ሰአታት በላይ  ተሰልፈው   ተራቸው እስኪደርስ መጠባበቅ ነበረባቸው፡፡ አነዚያ

Wednesday 13 March 2013

መንግስት ታላቁን የአፋር ኡለማ ሊያስር ነው! ድምፃችን ይሰማ

አፋሮች ትግሉን መቀላቀላቸው ተከትሎ ታላቁ የሀይማኖት መሪ ሸህ መሀመድ አወል ሃይታንን ለማሰር ፌዴራል ፖሊስ እየተጠራ እንደሆነ ታወቀ::
በአፋር ህዝብ ዘንድ እንደ አባት የሚታዩትን ታላቁን ዐሊም ሸህ መሀመድ አወል ሀይታንን ለማሰር መንግስት እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ ታወቀ፡፡ መንግስት ይህን እርምጃ ሊወስድ ያሰበው ለወትሮውም ቢሆን ለዲኑ ቀናኢ መሆኑ የሚታወቀው የአፋር ህዝብ በአሁን ሰዐት በዲኑ ላይ እየደረሰ ያለውን ጭቆና ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን መቃወም በመጀመሩ ነው፡፡ ሆኖም ግን የአፋር ነዋሪዎች እንደሚሉት የአፋር ህዝብ ስለ ዲኑና ስለ ማንነቱ ጠንቅቆ ያወቀበት ደረጃ ላይ በመድረሱ የትኛውንም አይነት ጭቆና ለመቀበል ፍቃደኛ አይደለም፤ ለዚህም ተቃውሞውን ተቀላቅሏል፡፡ የአፋር ህዝብ ከጊዜ ወደ ጊዜ መንቃቱ ያሰጋው መንግስት በበኩሉ በህዝብ ዘንድ ትልቅ ክብር ያላቸውን ሸህ ለማሰር እንደወሰነ፣ ይህ ደግሞ ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍለው እየተነገረ ነው፡፡

መነገር ያለበት ቁጥር አምስት “መሪዎቻንን የት አሉ?”

እኔ ምን አገባኝ የምትለው ሐረግ፣
እሱ ነው ሃገሬን ያረዳት እንደበግ፣
የሚል ግጥም ልጽፍ፣
ስሜት አንዘርዝሮኝ ብድግ አልኩኝና፣
ምን አገባኝ ብዬ ቁጭ አልኩ እንደገና ።
ኑረዲን ዒሣ
ጀርመን ፍራንክፈርት በታማኝ በየነ ስብሰባ ታምሳ ከረመች። ከብዙ ጊዜ በኋላ እንደገና ብዙ የፍራንክፈርት አካባባቢ ነዋሪዎች ተገናኝን። አልፎም ተርፎም ችግራችንን ተወያየን። በዚሁ አጋጣሚ ይህንን ዝግጅት ላዘጋጁት ለወ/ሮ አሳየሽኝና ለአቶ ጥላሁን ምስጋናየን በግሌ አቀርባለሁ።
ብዙ ተናጋሪዎች ፣ ብዙ ምርጥ ዝግጅቶች ስለነበሩ በደስታ ስንከታተል ቆየን። በመጨረሻም ታማኝ ንግግሩን ጀመረ። እኔ ማነኝ? በሚል ነበር የጀመረው። ራሱን ዝቅ አድርጎ ሃገራችን የመሪ እጦትን እንደደረሰባት አስረዳን። እሱ ስለመሪ እጦት ሲያስረዳን እኔ በሃሳብ ፍራንክፈረት ያስተናገደቻቸውን <<መሪዎቻችን>> አስባቸው ነበር። የመጀመሪው ስብሰባ የኢንጅነር ኃይሉ ሻውል ነበር። ከዛ በኋላ ብዙ ስብሰባዎች አድርገናል። ከብዙ አድካሚ ጉዞ በኋላ ነው ዛሬ በታናሽ ወንድም ታማኝ ስብሰባ ላይ የተገኘነው።

Tuesday 12 March 2013

‎! ….. የህወሓት ጉባኤ ምልመላ ፈተና ገጠመው ….!

ባለፈው በህወሓት ኣመራር በተፈጠረው ኣለመግባባት ምክንያት ሌላኛው ቡድን ለማሸነፍ ሲባል የነ ኣባይ ወልዱ ቡድን በተመረጡ የትግራይ ከተሞች በመንቀሳቀስ ለህወሓት ጉባኤ የሚሳተፉ ታማኝ የተባሉ፣ የደም ትሥሥር ያላቸው፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሆኑና በህወሓት ታሪክ የመቃወም መንፈስ ኣሳይተው የማያውቁ ካድሬዎች በከፍተኛ ጥንቃቄ መመልመላቸው ፅፌ ነበር።

ኣሁን ከህወሓት መንደር ያገኘሁት መረጃ እንደሚያመለክተው ደግሞ ኣባይ ወልዱ የመለመላቸው የጉባኤ ተሳታፊዎች በሌሎች የህወሓት ኣባላት ፈተና ገጥሟቸዋል። በጉባኤው ለመሳተፍ ያልተመለመሉ የህወሓት ኣባላት (በነ ኣርከበ ዕቁባይ ደጋፊዎች ተነሳሽነት በመታገዝ) ያኮረፉ ሲሆን በተሳታፊዎች ምልመላ ወገንተኝነት ጥያቄ ኣስነስተዋል። 


እነዚህ ያልተመለመሉ የህወሓት ኣባላት የምልመላው ሂደት በመቃወም በነ ኣባይ ወልዱ በተመለመሉ (በጉባኤው እንዲሳተፉ በተመረጡ ኣባላት) ላይ የተናጠል እርምጃ እንደሚወስዱና ቡድኑ ካሸነፈ ከህወሓት ኣባልነታቸው ራሳቸው እንደሚያገሉ ኣሳውቀዋል። የተመለመሉ ኣባላትም የተለያየ ዛቻና መገለል እየደረሰባቸው በመሆኑ ብዙዎቹ በጉባኤው ለመሳተፍ እንደ ማይፈልጉ እያሳወቁ ይገኛሉ።

ከእሁድ እስከ እሁድ (የሳምንቱ አጫጭር ዜናዎች)


ድርቅ ጦር እያማዘዘ ነው
የሟቾች ቁጥር ተደብቋል
በምስራቅና በምዕራብ ሃረርጌ ድርቅ በመግባቱ አርሶ አደሮች ከብቶቻቸውን በርካሽ ዋጋ ለመሸጥ መገደዳቸውን ዶይች ቬለ ሬዲዮ የአሜሪካን የርዳታ ድርጅት USAIDን ጠቅሶ ዘገበ። የድርጅቱ የምግብ አቅርቦት ተንታኝ ብሬክ ስታበረር እንዳሉት በአካባቢው የተከሰተው ድርቅ በሶማሊና በኦሮሞ አርብቶ አደሮች መካከል ግጭት አስከትሏል።
በተፈጠረው የውሃ ችግር ምክንያት ከብቶቻቸውን ውሃና ግጦሽ ፍለጋ ይዘው በሚሄዱ አርብቶ አደሮች መካከል የይገባኝልና ውሃና የግጦሹ ሳር ያልቃል በሚል ግጭት ተነስቷል። ተንታኙን የጠቀሰው ሬዲዮ በግጭቱ ስለደረሰው ቀውስ ያለው ነገር ባይኖርም ከተለያዩ ወገኖች የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በሶማሊና ኦሮሞ አርብቶ አደሮች መካከል በተከሰተው ግጭት ከሰባ የማያንሱ ሰዎች ተገድለዋል።

Monday 11 March 2013

“በፌዴራል ተደብድባችሁ ትባረራላችሁ!”


“አማራ መሆን ወንጀል ነው? የሌሎች ብሔረሰብ አባላት በፈለጉበት ክልልና ስፍራ ይኖራሉ። አማራ ክልል ውስጥ ሰፊ መሬት ወስደው የሚኖሩ አሉ፤ የሚነካቸው የለም። አማራው እየተመረጠ ለስደት፣ ለመከራ፣ ለእንግልት ይዳረጋል? እስከመቼ በዚህ ይቀጥላል? ክልሉን እንመራለን፣ የአማራ ህዝብ ወኪል ነን የሚሉ የት ናቸው? ያሳዝናል፣ ለአማራው አልቅሱ፣ ለአማራው አንቡ፣ አማራው አለቀ …”  ሲል በስልክ ለጎልጉል አስተያየቱን ሰጠ። መናገር አይችልም፤ ሲቃ ልሳኑንን አንቆ ይዞታል።
ከዓመታት በፊት መተከል ዞን ፓዌ የተካሄደውን ያነሳል። 1984 – 85 ፓዌ መንደር አራት በሚባለው የገበያ ቦታ እየገበዩ የነበሩ የአማራ ተወላጆች ያላሰቡት ደረሰባቸው። በድንገት ገበያው ታወከ። የቻሉትን በቀስት፣ ሌላውን በጥይት ለቀሙት። 56 ሰዎች በቅጽበት ተረሸኑ። ይህ ሁሉ ሲደረግ አገር የሚመሩት ባለስልጣኖች ድምጻቸውን አላሰሙም ነበር። አሁንም በተቆራረጠ አንደበት አስተያየቱን ቀጠለ።

The Meles Zenawi Harekat


I just finished Asgede Gebre Selassie’s rebuttal under ” Meles Zenawi from Dedebit to Senebete” a thirty eight years of the late Meles Zelawi lie and murder billed as his “legacy” on eighty page Propaganda Piece wrote by Bereket Simoan and Addissu Legesse to keep the Meles legacy for the next fifty years on the way keeping power and wealth under few Woyane anti Ethiopia cliques.
The 6 million propaganda copy was sold for Woyane members and supporters for 100 Bir each. Government workers were forced to buy. For the rest of us who wants to know what is in the book you have to read Asegede’s master piece posted on ethiomedia.com. “The Meles Harekat” is totally a fabrication like “Jehadawi Harekat”. The latter is exposed by the Ethiopian Muslims massive rally last month and we should commend Ato Asgede for writing the piece exposing “The Meles Harekat “.

እኛና እነሱ – የሁለት ሀገር ሰዎች ነን ከሥርጉተ ሥላሴ 10.03.2013


እም! ብዬ እያማጥኩ ጀመርኩት።

እኛ ማነን? እኛ የተቀመምንበት ኢትዮጵያዊነት የሚያንገበግበን። ችግሯ – ችግራችን፤ ዕንባዋ – ዕንባችን፤ መከፈቷ – መከፈታችን፤ ጉስቁልናዋ – ጉስቁልናችን፤ አንገት መድፋቷ ሃዘናችን የሆነው በዬትኛውም ዓለም የምንገኝ ልጆቿ ነን። በወያኔ መዳፍ ውስጥ አሳሩን በማዬት የሚገኘው ከስሜን እስከ ደቡብ ጫፍ፤ – ከዱቡብ ጫፍ እስከ ምዕራብ ጫፍ፤ ከምዕራብ ጫፍ እስከ ምስራቅ ጫፍ የሚገኝ ህዝብ ለሀገሩ ልዩ መለእነሱስ? „የደላው ገንፎ ያላምጣል“ እንዲሉ ከማህደረ – ኢትዮጵያዊነት ትንሽ ልቅላቂ ያልፈጠረላቸው፤ አለቶች … በዕንባ ላይ ይሾማሉ፤ ይሸለማሉ …. ልጆቻቸውን አንደላቅው ያሰተምራሉ፤ ሲሰኛቸው ውጬ ልከው ዶላር አፍሰው ያዝመነምናሉ።