No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Thursday 18 July 2013

! …. ትንሽ ስለ ዓረና ትግራይ ፓርቲ …….! Abraha Desta


ዓረና ትግራይ ፓርቲ ህዝባዊ ስብሰባ ጠራ

ፓርቲው ለእሁድ ሓምሌ 14, 2005 ዓም በመቐለ ማዘጋጃቤት አዳራሽ ህዝባዊ ስብሰባ መጥራቱ ተሰምቷል። ፓርቲው ‘አሉ’ በሚላቸው የህዝብ ችግሮች (ኑሮ ውድነት፣ የወጣቶች ስደት፣ የግብር አከፋፈል ችግሮችና የሙስና ሁኔታ፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና የመሳሰሉት የህዝብ ችግሮችና በዓረና ትግራይ የሚቀርቡ አማራጭ መፍትሔ ሓሳቦች ከመቐለና አከባቢው ህዝብ ነዋሪዎች መወያየት እንደሚፈልግ አስታውቋል። ሁላችን ተጋብዘናል፤ እንሳተፋለን።

ስንሳተፍ ግን ምን እንጠብቃለን? ዓረናዎች የህዝብ ችግሮችና የመፍትሔ አማራጫቸውን ሲነግሩን የህወሓት ደጋፊዎች (መሳተፋቸው አይቀርም ከሚል ነው) ደግሞ ‘ እናንተ ዓረናዎች እኮ ያው ናችሁ። ህወሓት ነበራቹ። ያኔ ለውጥ አላመጣችሁም።’ የሚል የተለመደ የፕሮፓጋንዳ ስትራተጂ መጠቀማቸው አይቀርም።

እኔም እላቸዋለሁ፡ አዎ! አብዛኛው የትግራይ ህዝብ የህወሓት ታጋይ ነበር፤ የህወሓት ፓርቲ አመራር አባል ግን አልነበረም። እነኚህ የዓረና አባላትም የትግራይ ህዝብ አባላት እስከሆኑ ድረስ የህወሓት ታጋዮች ነበሩ። የህወሓት ታጋይ መሆን በራሱ ስሕተት አይደለም። ህወሓት እንደ ትግልና እንደ ገዢ መደብ የተለያዩ ናቸው።

መንግስት ያደረሰበትን ሰቆቃ በፍኖተ ነፃነት ያጋለጠው ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ የገባበት ጠፍቷል



ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ የገባበት ጠፋ

ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት በመንግስት የደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በማዕከላዊና ዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ የደረሰበትን በደል ይፋ ቢያደርግ እንደሚገድሉት እንዳስጠነቀቁት ለፍኖተ ነፃነት አስረድቶ ነበር::

ግልጽ ደብዳቤ ለሃይሌ ገብረሥላሴ ከአበበ ገላው


ውድ አትሌት ሃይሌ፣ ከነመላው ቤተሰብህ እንደምን ከርመሃል? ልጆቹ እንዴት ናቸው፣ አለምስ እንዴት ሰንብታለች?
ሰሞኑን የወዳጅ የዘመድ ምክር አላዳምጥ ብለህ እንደነ ጋሼ ግርማና ጋሼ ሃይለማርያም ደሳለኝ የህወሃቶች አሻንጉሊት መሆን
እንዳማረህ ስሰማ በጣም ተገረምኩ። በመላው አለም ዝና ያተረፍክበትን እሩጫ ትተህ “ቤተመንግስት” ወይንም “ፓርላማ” ቁጭ ብለህ
ዝንብ ማባረር ምን ይጠቅመኛል ብለህ ነው? አንተም እንደነጋሼ ግርማና ሀይለማሪያም በቁምህ ከመሞትህ በፊት ምክሬን ባትሰማ
እንኳን ለማንኛውም ይቺን አጠር ያለች ጦማር ልጽፍልህ ወሰንኩ።
እኔ ያቺን “ሪከርድ” የሰበርክባትን ቲሸርት
ነፍሳቸውን ይማርና ለዛ ህዝብ ላፈኑ፣ ላሰቃዩ፣
ለረገጡና ለጨረሱ፣ እንኳን በቁማቸው ሞተውም
ላስመረሩን የሂትለርና የሞሶሊኒ ግልባጭ
በአደባባይ ስትሸልም መካሪ ማጣትህን
ገምቻለሁ። ግለሰቡ መሸለም ሳይሆን ተይዘው
እንደ ናዚዎቹ ኑረንበርግ ለፍርድ መቅረብ
ይገባቸው እንደነበር ጠፍቶህ ነበር ማለት
አይቻለኝም። ግን ሃያሉ ፈጣሪ ፍርዱን እንደማያዘገይ አሳየን።

Wednesday 17 July 2013

ከኦሮሞ ፖለቲካ ወደ ጃዋር ፖለቲካ? (ከመስፍን ነጋሽ )

01
ወንድሜ ጃዋር (Jawar Mohamed) ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በኦሮሞ ፖለቲካ እና አሁን ደግሞ ስለኦሮሞ-ኢስላም ያቀረባቸው ንግግሮች ኮርኳሪ ሆነዋል። ኮርኳሪነታቸው የሚመነጨው ግን ሐሳቦች አዲስ ስለሆኑ አይደለም፤ በአቀራረባቸውም ቢሆን ያልተለመዱ አይደሉም። “የአግራሞቱ” ወይም የንዴቱ ምንጭ ጃዋር የገነባው ወይም እየገነባው የመሰለን የፖለቲካ ማንነት እና በቅርብ ያንጸባረቃቸው አቋሞቹ እጅግ የሚቃረኑ ስለሚመስሉ ነው።
የኢትዮጵያን ፖለቲካ ውስብስብ ከሚያደርጉት ቁልፍ ጉዳዮች አንዱ የኦሮሞ ፖለቲካ ነው። ኢትዮጵያ ዜጎች ቢያንስ በመጠኑ ሐሳባቸውን በነጻነት የሚለዋወጡባት አገር ብትሆን ኖሮ ጉዳዩን ነጋ ጠባ በተነጋገርንበት፣ በተከራከርንበት ነበር። ይህ ባለመሆኑ ግን ከትልቁ የኦሮሞ ጉዳይ ይልቅ ጃዋር የተነፈሳት አንድ አረፍተ ነገር የበለጠ ቁም ነገር ያላት ሆና ተቆጠረች። መፍትሔው ጃዋርን ማውገዝ አይመስለኝም፤ ስለኦሮሞ ፖለቲካ መነጋገርና መደማመጥ ያስፈልጋል።

“የአዲስ አበባ መሪ ፕላን የኦሮሞን መሬት ለመንጠቅና ለማፈናቀል የታቀደ ሴራ ነው” ኦፌኮ

ኦህዴድ በአዲስ አበባ መሪ ፕላን ላይ
የአመራሩን ብዥታ ሊያጠራ ነው
“የአዲስ አበባ መሪ ፕላን
የኦሮሞን መሬት ለመንጠቅና ለማፈናቀል የታቀደ ሴራ ነው”
ኦፌኮ
 
በዘሪሁን ሙሉጌታ
የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ከአዲስ አበባ መሪ ፕላን ጋር በተያያዘ በዙሪያዋ ካሉ ከተሞች ጋር በቀጣይ ሊኖር ስለሚችለው ግንኙነት በተመለከተ የድርጅቱ አመራርን ብዥታ ለማጥራት እንደሚንቀሳቀስ አስታወቀ። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) በበኩሉ የአዲስ አበባ መሪ ፕላን የኦሮሞን መሬት ለመንጠቅና ለማፈናቀል የታቀደ ሴራ ነው ብሏል።

EU delegation: Ethiopia should release jailed journalists and activists

July 17, 2013
by Associated Press
A European Union parliament delegation in EthiopiaADDIS ABABA, Ethiopia — A European Union parliament delegation on Wednesday called on Ethiopia’s government to release jailed journalists and activists, but in a sign the call may not be heeded the delegation was denied from visiting a prison it had been approved to see.
The head of the delegation, Barbara Lochbihler, said Ethiopia is jailing journalists and activists for “exercising their legitimate right to freedoms of expression, association and religion.” The group is concerned by reports of misuse of the country’s anti-terrorism legislation to stifle dissent, she said.
“Despite the country’s excellent constitution, we note flaws in the impartiality of the judicial system,” Lochbihler told journalists at a press conference Wednesday.