No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Thursday 18 July 2013

መንግስት ያደረሰበትን ሰቆቃ በፍኖተ ነፃነት ያጋለጠው ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ የገባበት ጠፍቷል



ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ የገባበት ጠፋ

ወጣት ተስፋዬ ተካልኝ መኮንን ፤ አርሲ አርባ ጉጉ ተወልዶ በ1998 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሶሲዮሎጂ ተመርቋል፡፡ በ2000 ዓ.ም በባህልና ቱሪዝም ሚ/ር በሲኒየር ካልቸራል ኤክስፐርትነት የስራ መደብ እስከ ሚያዝያ 2003 ሰርቷል፡፡ ሚያዝያ 12 ቀን 2003 ዓ.ም በግልፅ ባልተረዳው ምክንያት በመንግስት የደህንነት ሀይሎች ተያዞ ለ23 ወር በማዕከላዊና ዝዋይ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ እየተፈፀመበት መቆየቱን ይናገራል፡፡ መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም ከእስራት ሲለቀቅም አንድ ጊዜም እንኳን ፍርድ ቤት እንዳልቀረበ ለፍኖተ ነፃነት አስረድቷል፡፡ የደረሰበትን በደል ይፋ ቢያደርግ እንደሚገድሉት እንዳስጠነቀቁት ለፍኖተ ነፃነት አስረድቶ ነበር::


አሁን ተስፋዬ ተካልኝ በየቀኑ ይመላለስበት ከነበረዉ የአንድነት ቢሮ ከቀረ አንድ ሳምንት ሞልቶታል::የግል ተንቀሳቃሽ ስልኩም አይሰራም:: ተስፋዬ ተካልኝ ያለበትን ወይም የደረሰበትን አዉቃለሁ የሚል አንድ ይበል::

ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት

No comments:

Post a Comment