No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Saturday 19 January 2013

አሜሪካ በአፍሪካ ወታደራዊ የበላይነቷን ልታረጋግጥ ነው!


ፕሮግራሙን ለማስፈጸም 35 አገሮች ተመርጠዋል
አዲስ በተያዘው የአውጳውያን ዓመት አሜሪካ በአፍሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ የበላይነትን ሊያረጋግጥላት የሚችል ፕሮግራም ነድፋለች፡፡ ከሦስት ሳምንታት በፊት ይፋ የሆነውን ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ ላይ የተነደፈውን ዕቅድ የሚያስፈጽሙ 35 የአፍሪካ አገሮችም ተመርጠዋል፡፡
ምንም እንኳን ዜናው ይፋ ከሆነ የቆየ ቢሆንም የአሜሪካንን የመከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) እንዲመሩ የታሰቡት ሪፓብሊካኑ ቸክ ሔግል ቀዳሚ ተወዳዳሪ መሆናቸው እስከሚገለጽ ድረስ የብዙዎችን ቀልብ አልሳበም ነበር፡፡ የአሜሪካንን ጦር ሠራዊት በየአገሩ በማዝመት ጉዳይ ላይ ጽኑ የተቃውሞ አስተሳሰብ የሚከተሉት ሔግል እንዲህ ዓይነቱን ፕሮግራም ለማስፈጸም ገጣሚ ሚኒስትር እንደሚሆኑ በሰፊው እየተነገረ ነው፡፡
የመከላከያ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ይፋ እንዳደረገው በአፍሪካ በየጊዜው እያገረሸ የሄደውን የአሸባሪዎች እንቅስቃሴ ለመቆጣጠርና ሌሎች በክፍለ አህጉሩ የሚነሱ ቀውሶችን ለመከላከል የሚል ዕቅድ የወጣለት ፕሮግራም በያዝነው የአውሮጳውያን ዓመት ተግባራዊ ይሆናል፡፡ ይህ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ፕሮግራም የሚያተኩረው ጦርነት ወይም ሁከት በተፈጠረ ጊዜ የአሜሪካንን ወታደሮች በየቦታው ከመላክ ይልቅ አፍሪካውያንን ለራሳቸው ችግር ወታደራዊ ዕርምጃ ለመውሰድ እንዲችሉ የሚያደርግ ነው፡፡ ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ እንዲያስችል የአሜሪካ ወታደራዊ መኮንኖች ለአፍሪካውያኑ የተለያየ ወታደራዊ ሥልጠና ለመስጠት ወደዚያው ያመራሉ፡፡
መቀመጫውን በካንሳስ ጠቅላይ ግዛት የራይሌ ምሽግ ባደረገው በ1ኛው የእግረኛ ዲቪዚዮን ሥር የሚገኘው ሁለተኛው ብርጌድ (ወይም በልዩ ስሙ ጩቤ ብርጌድ) የሚውጣጡ አሰልጣኝ መኮንኖች በሊቢያ፣ ሱዳን፣ አልጄሪያና ኒጀር የሚገኙ የአልቃይዳ ደጋፊዎችን ዋና ዒላማ በማድረግ በቅድሚያ እንደሚንቀሳቀሱ ፎክስ ኒውስ ዘግቧል፡፡ ከአልሸባብ ሚሊሻዎች ጋር ጦር የገጠሙትን ኬኒያና ዑጋንዳንም እንደሚያግዙ ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡
በሚያዚያ 2000ዓም የአሜሪካ መኮንኖች በኢትዮጵያ ሥልጠና ሲሰጡ::(የፎቶው ባለቤት:US Army Africa's photostream)
ይኸው በቡድን እየተደራጀ ሥልጠና የሚሰጠው የወታደራዊ መኮንኖች ስብስብ በአንዳንድ ቦታዎች በጥቂት መኮንኖች ብቻ በሌሎች አገሮች ደግሞ በመቶዎች በመሆን ሥልጠናውን እንደሚሰጡ ታውቋል፡፡ መኮንኖቹ ሥልጠናውን ለመስጠት በሚቆዩበት ጊዜያት ሁሉ የባህል፣ የአካባቢ፣ የቋንቋ፣ ወዘተ ችግር እንዳይገጥማቸው የሚላኩበትን አገር በተመለከተ የአጭር ጊዜ ሥልጠና እየተሰጣቸው ይገኛል፡፡ አላላካቸውም ጥቂት በጥቂት ይሆናል፡፡
በፕሮግራሙ ከፍተኛ ሥልጣን ያላቸው ጄኔራል ሬይመንድ ዖዲዪርኖ አሜሪካ ከዚህ በፊት የነበራትንና አሁን በአዲሱ ፕሮገራም የሚኖራትን ሚና ሲገልጹ “ከዚህ በፊት ስንከተል የነበረው ስትፈልጉን ጥሩን ዓይነት ነበር፡፡ አሁን ግን ከዚያ ባለፈ መልኩ” እንደሚሆንና ከዚህ በፊት ከነበረው አሠራር በስፋት የተለየ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የአፍሪካን የዕዝ ማዕከል (አፍሪኮም) እንዲመሩ የታጩት ጄኔራል ዴቪድ ሮድሪጌዝ በበኩላቸው ሲናገሩ “እኛ እዚያ የምንሄደው የእኛ አሠራር እንዴት እንደሆነ ልናሳያቸው አይደለም፤ የራሳቸው አሠራር እንዴት ተግባራዊ መሆን እንደሚችል ለማስተማር ነው፡፡ የጦር ሠራዊታቸው አሁን ያለበትን ሁኔታ ከተመለከትን በኋላ የት ደረጃ ላይ መድረስ እንዳለበት እናሠለጥናቸዋልን፤ እናዘጋጃቸዋለን” ብለዋል፡፡
ዴሞክራሲ፣ መልካም አስተዳደር፣ ሰብዓዊ መብት ጥበቃ፣ ወዘተ ብርቅ በሆነባት አፍሪካ ይህ ዓይነቱ የአሜሪካ ወታደራዊ ድጋፍ በአምባገነኖች የተሞላውን አህጉር የበለጠ ጨለማና ተስፋ ቢስ እንደሚያደርገው የአፍሪካ ጉዳይ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ለአብዛኛዎቹ አምባገነን መሪዎች ህዝባቸውን ለመርገጥና በሥልጣን ለመቆየት የአሜሪካ ወዳጅ መሆን እንዲሁም ይህንን ዓይነት በቀዳሚነት የአሜሪካንን ጥቅም የሚያስጠብቅ ወታደራዊ የበላይነት በአገራቸው እንዲካሄድ መፍቀድ ቀላሉ መንገድ እንደሚሆናቸው አስተያየት ተሰጥቶበታል፡፡
ሟቹ ጠ/ሚ/ር በአገር ውስጥ የነበረውን የፖለቲካ ውጥረት ለማርገብ ሶማሊያንን በመውረር የአሜሪካ ጠንካራ ወዳጅ በመሆን በሥልጣን ለመቆየት አማራጭ እንዳደረጉት አሁን ያሉትም ሆነ ሌሎቹ አምባገነን መሪዎች ይህንኑ መስመር እንደሚከተሉ ከተለያዩ የዜና ምንጮች የሰበሰብነው የአፍሪካውያን ምሁራን አስተያየት ይጠቁማል፡፡ ይህ ዓይነቱ አካሄድም ከኢትዮጵያ ውጪ ያሉትን አሸባሪዎች ሳይሆን በአገር ውስጥ የዴሞክራሲ፣ የመብት፣ ወዘተ ጥያቄ የሚያነሱ ሁሉ በአሸባሪነት እየተፈረጁ ለሥቃይ የተዳረጉበት፤ መብት ረገጣው የተስፋፋበት እና ምዕራባውያን ከዝምታ ወይም ከውግዘት ያላለፈ ጠንካራ እርምጃ ሊወስዱ የማይፈልጉበት ደረጃ ላይ እንዲደርሱ አድርጓቸዋል፡፡
የአፍሪካንን ጉዳይ በቅርብ በሚከታተሉ ዘንድ ልዩ ትኩረት የተሰጠው ይኸው የአሜሪካ ወታደራዊ የበላይነት በይፋ ከተነገረው አሸባሪዎችን የማጥቃትና የመቆጣጠር ዋና ዓላማ ሌላ ዕቅድ አለው የሚል የመከራከሪያ ነጥብ ቀርቦበታል፡፡ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከአፍሪካ አምባገነን መሪዎች ጋር የቅርብ ግንኙነት በማድረግ አፍሪካን እየተቆጣጠረች የመጣችውን የቻይናን እንቅስቃሴ በቅርብ ሆኖ ለመከታተል እንዲያመች ነው የሚል ጠንከር ያለ አስተያየት በእነዚሁ  ወገኖች ተሰጥቶበታል፡፡ ከአሜሪካ ጋር በወታደራዊ ስምምነት በመተባበር ወይም ከቻይና ጋር በኢኮኖሚ በመተሳሰር በየትኛውም መልኩ ቢሆን የአፍሪካ አምባገነኖች የአገዛዝ ዘመናቸውን የሚያረዝሙበት ምቹ አማራጭ ማግኘታቸው ጨምሮ ተገልጾዋል፡፡
ፕሮግራሙን በተመለከተ ከአፍሪኮም እስካሁን ወደ መቶ የሚጠጉ የምደባ ጥያቄዎች መቅረቡን የተናገረው የዜና ዘገባ ዝግጁ የሆኑትና ሥልጠናቸውን ያጠናቀቁት የመጀመሪያዎቹ ወታደራዊ መኮንኖች በጥቂት ወራት ውስጥ ወደ አፍሪካ እንደሚያቀኑና ጨምሮ አስታውቋል፡፡                                                 (ፎቶ፡ sott.net)
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡


Friday 18 January 2013

BREAKING NEWS: Ethiopia’s minority junta to hijack the 2013 Nations Cup

Preparation under way to immortalize the late Ethiopian evil fuehrer at 2013 AFCON tournament
Ethiopian embassy sources in Pretoria have told the Horn Times that over 10,000 t-shirts bearing the late poisonous tyrant Meles Zenawi’s image have been printed and thousands of refugees are recruited by well known TPLF cadres to don them. The refugees will be bused to Mbombela stadium for free where the black lions would face the defending champions, the copper bullets of Zambia.

ሰበር ዜና፣ መንግስት በምስክር እጦት ጭንቅ ውስጥ ገብቷል፡፡


የብዙዎች ምላሽ ‹‹በሐሰት አንመሰክርም›› የሚል ሆኗል፡፡

በእስር ላይ የሚገኙ መሪዎቻችን እና ሌሎች ወንድሞቻችንን በአሸባሪነት ከስሶ ሲያንገላታ የቆየው መንግስት በምስክር እጦት ችግር ውስጥ መግባቱ ታወቀ፡፡ መንግስት ኮሚቴዎቻችን ላይ በመሰረተው ክስ በሐሰት ሊያስመሰክራቸው ያዘጋጃቸው 197 (አንድ መቶ ዘጠና ሰባት) ሰዎች መኖራቸውን ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም የተገለጸውን ቁጥር ያህል ምስክሮች ማግኘት አልቻለም፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው ለምስክርነት የታሰቡት ብዙዎቹ ግለሰቦች ምስክር ለመሆን ፈጽሞ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ነው፡፡ መሪዎቻችን ባልዋሉበት እና በማያውቁት ወንጀል የከሰሳቸው መንግስት በየአካባቢው ‹‹ድጋፍ ይሰጡኛል፤ እተማመንባቸዋለሁ›› የሚላቸውን ግለሰቦች ለምስክርነት ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያደርግላቸውም በሐሰት አንመሰክርም የሚል ቆራጥ አቋም ማሳየታቸው ተሰምቷ፡ል፡

Thursday 17 January 2013

“በ2030 ከሚከሽፉ መንግሥታት አንዷ ኢትዮጵያ ነች”ዘገባው የ15 አገራትን ዝርዝር አውጥቷል

የአሜሪካ የብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ2030 የሚከሽፉ 15 መንግሥታትን (failed states) ዝርዝር አውጥቷል፡፡ “በግጭት መብዛትና በአካባቢ ጥበቃ ቀውስ ምክንያት” ይከሽፋሉ ተብለው ከተተነበዩት የአፍሪካ፣ የእስያና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡
እጅግ የነጠረ፣ ያልተዛባና የተጠና ዘገባ ለአሜሪካ የስለላ ተቋማት፣ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አውጪዎችና ለዓለምዓቀፍ ግንኙነት ተመራማሪዎች በማውጣት የታወቀው የአሜሪካ ብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት ከተቋቋመ በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ምክርቤቱ በሚያወጣቸው ዘገባዎች የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የተለያዩ መ/ቤቶች ተጽዕኖ እንደማያደርጉበት የሚናገር ሲሆን፤ ዘገባዎቹንም ከአድልዎ እና ከአሜሪካ መንግሥት አቋም ነጻ በመሆን እንደሚያዘጋጃቸው ይናገራል፡፡

« ፍቅረኛሞቹ» አዜብ መስፍንና ብርሃነ ኪዳነማርያም(ከኢየሩሳሌም አርአያ)


አዜብ መስፍንን ከሱዳን አምጥቶ ሕወሓትን እንዲቀላቀሉ ያደረገ ነው። የፍቅር ግንኙነትም ነበራቸው። ይህ ሰው ብርሃነ ኪዳነማርያም (በቅፅል ስሙ ብርሃነ-ማረት) ነው። አዜብና ብርሃነ ድርጅቱን ሲቀላቀሉ የተቀበሏቸው አቶ አስገደ ገ/ስላሴ (አሁን የአረና አባል) ነበሩ። ጥቂት የበላይ አመራሮች በሁለቱ የፍቅር ግንኙነት ዙሪያ መከሩ። ከዛም የብርሃነና የአዜብ ግንኙነት እንዲቋረጥ በማድረግ ከለያዩዋቸው በኋላ ከመለስ ዜናዊ ጋር አዜብ እንዲጠቃለሉ ሆነ። (በነገራችን ላይ አንዳንድ ወገኖች አዜብና ሟቹ ክንፈ ገ/መድህን በጫካ ግንኙነት እንደነበራቸው ተደርጎ የሚነገረው ከእውነት የራቀ እንደሆነ የቅርብ ታማኝ ምንጮች ይገልፃሉ፤)
ወደ ዋናው ርዕሰ ጉዳይ እናምራ፥ በሕወሓት ውስጥ አድፍጠው መሰሪ ተግባር ከሚፈፅሙት አንዱ ነው ተብሎ በፓርቲው ወገኖች የሚፈረጀው ብርሃነ ኪ/ማርያም (ብርሃነ-ማረት) ማንነትና አደገኛ አካሄድ ምን እንደሚመስል ከላይ የተገለፀውን መንደርደሪያ ያስቀደሙ ታማኝ ምንጮች ተከታዩን ይላሉ።

Wednesday 16 January 2013

ኢትዮጵያ፤ የመዳኛ ወቅትና፤ የዕረቀሰላም ጊዜ


ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ
የረፖርተር ድሕረ ገፅ ሲዘግብ:በጎሳ ላይ የተመሰረተ ግጭት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሃል በመጸዳጃ ቤቶች፤ በቤተመጻህፍትና በመኝታ ቤት  ግድግዳ ላይ፤የተጻፉ አስፀያፊ ክብረነክ ጸሁፎች ከስድስት በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ለከፍተኛ የመቁሰል አደጋ ተጠቂ ዳርጓቸዋል:: በርካታዎችንም ለእስር አብቅቷል፡፡ ለላለፉት አሰርት ዓመታት፤በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሃል ግጭቶችን ሲያስነሱ ከርመዋል፡፡ ይህም መሰረታዊ ችግሩና መንስኤው አስተዳደራዊ ድክመት ነው፡፡ ከዚሁ ጋር በተመሳሳይ ባለፈው በእለተ ዕረቡ ጃንዋሪ 2 2013 የተቀሰቀሰው ግጭትም በተለይ በሁለት ጎሳዎች በኦሮሞና በትግራይ ተማሪዎች መሃል

Tuesday 15 January 2013

አዲስ አበባ ረክሳለች! ለጋ ህጻናትን ለባለስልጣናትና ባለሃብቶች ማቅረብ “ትርፋማ” ሆኗል


ትውልድ አምካኝ ቤቶችን፣ ትውልድ አምካኝ ደላሎችን፣ በህጻናት የወሲብ ንግድ ገንዘብ የሚሰበስቡትን፣ ማጥፋት ቀላል ነው። ግን ተጠቃሚዎቹ ህግ አስከባሪዎቹ፣ ህግ አወጪዎቹና ዋናዎቹ “የአገሪቱ ህዳሴ ባለቤቶች” የሚባሉት በመሆናቸው አይታሰብም። አንዳንድ ዝግ ቤቶች በሲቪል ጠባቂዎች የሚጠበቁ ናቸው። አንዳንዴ ቤተመንግስቱንና ሟቹን የቤተመንግስት ነዋሪ ይጠብቁ የነበሩት በፈረቃ ይታደሙባቸዋል።
ሃኪሞች፣ የህግ ባለሙያዎች፣ አገር የሚመሩት፣ ህግ የሚያስከብሩት፣ የመከላከያ ከፍተኛ መኮንኖች፣ አውራ ባለስልጣናት፣ ህዝብ ፊት ቀርበው በልማት ስም የሚምሉት ሃብታም ተብዬዎች፣ የፖሊስ የበላይ አመራሮች፣ የስለላ አውራ ሰዎች፣ አጫፋሪዎች፣ የአቻ ፓርቲ አመራሮችና መካከል ጥቂት የማይባሉ ከዳር እስከዳር መመሸጊያቸው ዝግ ቤቶች ናቸው። አንዳንዴም ከዝግ ቤቶች ፍራሽ ላይ ሆነው የፖለቲካ መመሪያ የሚሰጥበት አጋጣሚ አለ። ይህን አስደንጋጭ እውነት “መርከስ” ነው። አዲስ አበባ ይፋ አደረገችው እንጂ በየክልሉ ከተሞች የሚደረገው ተመሳሳይ ነው።

Temesgen Desalegn ‹‹አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›› ሁለት ወቅታዊ ጉዳዮች

1. ከመለስ ሞት በኋላ መረጋጋት የተሳነው ኢህአዴግ ከበርካታ ችግሮች ጋር ፊት ለፊት ተፋጧል፡፡ ከችግሮቹ በከፊልም የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ …በረከት ስምኦን የነበራው ተደማጭነት እየተሸረሸረ ነው፣ የበረከት ባለቤት የበረከትን መፅሃፍ ለመሸጥ (ገዥ ፍለጋ) በየተቋማቱ እየተንከራተቱ ነው፤ አዲሱ ለገሰ የተደማጭነት መስመሩን ‹‹ኢህአዴግን ለማጠናከር›› በሚል ምክንያት ይበልጥ እያደረጀ ነው፤ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከቀን ወደ ቀን በህወሓት ውስጥ ተሰሚነቱ እየጨመረ ነው፣ በእርግጥም ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የአስጊ ህመም ችግር የሌለባቸው ተብለው የሚመደቡት ...ደብረፅዮን፣ አባይ ፀሀዬና ቴውድሮስ አድሃኖም ናቸው፣ አቦይ ስብሃት ነጋ ‹‹መፈንቅለ ፓርቲ›› በህወሓት ውስጥ ለማድረግ ቀን ከለሌት እያሴሩ ነው፣ ከሁለት ወር በኋላ የሚደረገው የኢህአዴግ ጠቀላላ ጉባኤ አዲስ ነገር ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል፤ ኦህዴድ በሹም ሽር ሊናጥ ነው፣ አለማየሁ አቱምሳ በሩቅ ምስራቅ ለሚከታተለው ህክምና እስከአሁን ያለውንም ሆነ በቀጣይ የሚያስፈልገውን ወጪውን እየሸፈነ ያለው ሼክ መሀመድ አላሙዲ ነው፤ ለምን? አለማየሁ የመንግስት ባለስልጣን ነው፣ በተጨማሪም ሆን ተብሎ በተሰጠው መርዝ ነው ታማሚ የሆነው የሚባለውን ወሬ ይዘን፣ ከዚህ ጀርባ ማን ነው ያለው? የሚል ጥያቄ መቀርቡ አይቀርም (የሰማሁት መረጃ ጆሮ ያቃጥላል) ግን ለምን? ኩማ ደመቅሳ መልካም አስተዳደር ባለማስፈንና ሙስናን መቆጣጠር

ጥፋቱ የማን ነው? “ባድመ የኛ አይደለም!” በረከት ስምዖን

ኤርትራዊ ሆነው በኢትዮጵያ ከፍተኛ የስልጣን ሃላፊነት የተሸከሙት አቶ በረከት ስምዖን በኢትዮጵያ ላይ የሚፈርድ፣ ዜጎችን የሚያሸማቅቅ፣ ለአገራቸው የተሰውትን የሚያናንቅና በተለይም በውድ አገራቸው የሚመኩ ወገኖችን የሚያኮስስ ንግግር ማድረጋቸው በህወሃት ነባር ታጋዮች ዘንድ ቅሬታ ማስነሳቱ ታወቀ። አቶ ስዬ አብርሃ፣ አቶ ገብሩ አስራት፣ እነ አቶ ተወልደን በስም በመጥራት በኤርትራ ጉዳይ ላይ ጥፋተኛ ያደረጉት አቶ በረከት “አንድነትና አንድ አገር” የሻዕቢያ መዝሙር መሆኑን በመናገር ኢትዮጵያ ውስጥ መገንጠል ለሚፈልጉ ጊዜው ሲደርስ እንደ ኤርትራ መገንጠል መብታቸው መሆኑን ተናግረዋል።
በሚኒስትር ማዕረግ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ሃላፊ አቶ በረከት ይህንን የተናገሩት Eritrean Oppositions Arabic Paltalk በሚሰኝ የኤርትራ ተቃዋሚዎች የፓልቶክ መወያያ ክፍል እንግዳ ሆነው ባካሄዱት የጥያቄና መልስ ነው።

"Egypt has succeeded in stopping any funding to build Ethiopian Renaissance Dam" Egypt Minister of Water

Egypt State Information Service (Cairo)
Minister of Water Resources and Irrigation, Dr. Mohamed Baha'a El Din said in an interview with the official Chinese News Agency (Xinhua) on 12/1/2013 that Egypt will not sign the agreement of "Entebbe" signed by the Nile River upstream countries unless the conditions become suitable for downstream countries.
The Minister stressed that the agreement, without signing Cairo and Khartoum, is useless.