No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Thursday 11 April 2013

! ……. የትግራይ መምህራን እሮሮ ……………….!

በኢትዮዽያ ዩኒቨርስቲዎች እየሰለጠነ ያለው የሰው ሃይል (ከምረቃ በኋላ) ብዙ ችግሮች እንደሚፈታተኑት ይታወቃል። ከነዚህ ችግሮች አንዱ ‘ስራ ኣጥነት’ ነው። የስራ ኣጥነቱ ምንጭ ደግሞ የፖለቲካ ሙስና ነው።

ሙሁራን ዜጎች የመንግስት ስራ (በሚፈልጉት ዓይነት) የሚይዙት ባገኙት ውጤት ሳይሆን በዘመድ ኣዝመድ ነው። የስራ ዕድገት (የደመወዝ ጭማሪ) የሚያገኙት በስራ ብቃታቸው ሳይሆን በፖለቲካ ኣመለካከታቸው (ለገዢው ፓርቲ ባላቸው ቅርበት ወይ ታማኝነት) ነው።

ከዩኒቨርስቲ የተመረቁ ዜጎች የፖለቲካ ታማኝነታቸው ካላስመሰከሩ የኢኮኖሚ ሽብር ይደርሳቸዋል፤ ዕድገት ኣያገኙም ወይም ከስራ እስከማባረር ድረስ ይደርሳሉ። ይህም ሁኖ ግን ብዙ ‘ስራ ኣጦች’ ኣሉ። (በኢትዮዽያ ዉስጥ ያለው ስራ ኣጥነት ባብዛኛው በፍትሕ እጦት ምክንያት የሚፈጠር ነው።)

በትግራይ ክልል በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ መምህራን በፍትሕ ችግር፣ በኑሮ ውድነት እየተሰቃዩ ይገኛሉ። ክልሉ ለዜጎች ስራ ፈጥርያለሁ ባይ ነው። ግን ብዙ መምህራን ቅሬታቸው እየገለፁ ይገኛሉ።

ባለፈው ሳምንት ነው። የትግራይ ክልል መንግስት ከመቐለ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በትግራይ ላሉ መምህራን በመማር ማስተማር (ፔዳጎጂ) ላይ ያተኮረ ስልጠና ለመስጠት ከመጋቢት 27 እስከ ሚያዝያ 1, 2005 ዓም ቀነ ቀጠሮ ይዞ ነበር። ስልጠናው በሽረ፣ ዓድዋ፣ ውቅሮና ኣላማጣ ነበር እንዲካሄድ የታቀደው።

በስልጠናው የሚሳተፉ መምህራን 1615 ሲሆኑ ሁሉም በዲግሪ መርሃ ግብር የተመረቁ ናቸው። ስልጠናው በሚሰጥበት ግዜ ታድያ ችግር ተፈጠረ። መምህራኖቹ ደስተኞች ኣይደሉም። “ ከስልጠናው በፊት ጥያቄዎቻችን ይመለሱልን” ኣሉ። ለካ እነኚህ በዲግሪ የተመረቁ ሙሁራን የተቀጠሩት በዲፕሎማ ማዓርግ ነው። ደመወዛቸው የሚከፈል በዲፕሎማ እርከን ሲሆን በወር 1233 (Monthly Gross Salary) ብር ብቻ ነው።

ይገርማል። እንዲህ ነው ምርቋኖቻችን ከዲግሪ ወደ ዲፕሎማ ሲያድጉ። 1233 ብር ግብር ሲቀነስበት ስንት ይቀራል??? 1233 ብር የጫማ ዋጋ ነው ወይ ከቤት ኪራይ ኣያልፍም። በ1233 ብር ደመወዝ ምን ሊሰራ ይችላል? (ኑሮ ውድነቱ ግምት ውስጥ ኣስገቡ)። ኣስተማሪዎቹ ዲግሪ ተምረው በዲፕሎማ ሲቀጠሩ ምን ዓይነት ሞራል ይሰማቸው ይሆን? ምን በልተውስ ያስተምራሉ?



ሰው እንኳን ሳይበላ ሊያስተምር ሳይበላ መኖርም (መተኛት፣ መቀመጥ፣ መንቀሳቀስ) ኣይችልም። ስለዚህ በዚህ ሞራልና ደመወዝ በኣግባቡ ሊያስተምሩ ኣይችሉም። አንዴ ተጎድተዋል። ተማሪዎችም ይጎዳሉ፣ ምክንያቱም በኣግባቡ ሊማሩ ኣይችሉም። ሳይበሉ ስለ ፔዳጎጂ ሊማሩ??? ስለዚ ይሄ ኣካሄድ (መምህራን ደረጃቸው በመቀነስና በኣነስተኛ ደመወዝ እንዲያስተምሩ ማስገደድ) ትውልድን ይገድላል።

ባጠቃላይ በኣስተማሪዎቹ ተቃውሞ ምክንያት ስልጠናው ኣልተሳካም። መንግስት ዲግሪ ለያዙ ሰዎች 1233 ብር ብቻ ሲከፍል የባለስልጣናቱ ዘመዶች የሆኑ ግን (ዲግሪ እንኳ ሳይኖራቸው) በትእምት ከ100, 000 (መቶ ሺ) ብር በላይ (አንዳንድ ተጨማሪ ጥቅማጥቅሞች ሳይጨምር) እንደሚከፈላቸው ይታወቃል።

እስከ መቼ ይሆን በእንደዚህ ዓይነት ኣድልዎና ጭቆና የምንኖረው? እኔ ግን ይሄን ኣሰራር ኣልፈልገውም፣ እቃወመዋለሁኝ።
It is so!!!
source: ABRAHA DESTA FB BAGE.

No comments:

Post a Comment