No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Wednesday 29 May 2013

! …. ትንሽ ስለ ዳንኤል ብርሃነ …! by Abraha Desta

ዳንኤል (Daniel Berhane) የፌስቡክ ጓደኛዬ ነው። የኢህኣዴግ መንግስት ደግፈው ከሚፅፉ ሰዎች የተሻለ መከራከርያ ሓሳብ ማንሳት የሚችል ነው። ሞያው ራሱ እንደነገረን ጋዜጠኛ ነው። ከኢህኣዴግ ባለስልጣናት በቅርብ እንደሚገኝ (የአብዛኞቹ የግል ስልክ ቁጥር እንዳለው) እገሌ ጋ ደውዬ ነበር፣ እገሌ ስልኩ አያነሳም … ገለመሌ እያለ ከሚፅፋቸው ነገሮች መረዳት ይቻላል።

የሆነ ሁኖ ጥረቱ የሚመሰገን ነው።

እኔ ስለ ዳንኤል የሰማሁት የደህንነት (የሳይበር ሰላይ) መሆኑ፣ በበረከት ስምኦን ፍቃድ የተሰጠውና ድጋፍ የሚደረግለት (ስራው የግል ጋዜጠኝነት ሁኖ ወይ በማስመሰል የመንግስት አፈ ቀላጤ ተደርጎ ደመወዙ ከመንግስት ካዝና እንደሚከፈለው)ና ኢህኣዴጎች እንደሚተማመኑበት ነበር። ይህን መረጃ ግን እስካሁን አላመንኩትም ነበር (ደሞ አመንኩ አላመንኩ ምን ያደርግልኛል? እንደማንኛውም ዜጋ ሓሳቡ በነፃነት የመግለፅ መብት አለው’ኮ)። በዚህም ስለ ማንነቱ ጉዳዬን አላደርገውም።


እስቲ ዛሬ ስለ ሰው እናውራ። (ጓደኞቼ ሰለ ‘አንድ ግለሰብ’ ማውራት ትክክል አይደለም እንደምትሉኝ አልጠራጠርም። የሰውየው ማንነት ማወቅ ግን ለብዙ ሰዎች ደህንነት ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም ሰውዬው በትክክል የኢህኣዴግ የስለያ አባል ከሆነ ዳንኤል አንድ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን ‘ተቋም’ ነው ማለት ነው።)

በዛሬው ቀን በፌስቡክ ዎሉ ተለጥፎ ያየሁት (በአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚያስችለው ባች) ዳንኤል የኢህኣዴግ የደህንነት (ወይ ስለያ) ባልደርባ እንደሆነ የሚጠቁም ነገር አለ (ወይስ ማንኛውም ጋዜጠኛ ወደ የመሪዎች ስብሰባ ሲጋበዝ ፍቃድ የሚሰጠው በደህንነት ቢሮ በኩል ነው? መረጃ የለኝም። ስለዚህ እንድታስረዱኝ በትህትና ልጠይቅ።)

ስለዚ ዳንኤል (እንደ ጓደኛ) በጋዜጠኛ ወይስ በሰላይ እንወቅ ህ? (መቼም ቅር እንደማይልህ ተስፋ አደርጋለሁ፣ ምክንያቱም ጥያቄው አስፈላጊ ባይሆንም ሰው ስለ ጓደኛው ስራና ማንነት ለማወቅ ቢጠይቅ ነውር አይደለም።)

ወባና ሰላዮችን በጋራ እንከላከል።

It is so!!!
source:Abraha Desta fb page.

No comments:

Post a Comment