No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Monday 22 October 2012

በደቡብ ወሎ ዞን የተቃውሞ ሰልፍ መንገድ በመዝጋት ቀጥሎአል

557803_168065900000140_380620062_nበደጋን እና በገርባ ከተማ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በነቂስ ወጥቶ ተቃውሞ በማሰማትላይ ይገኛሉ፡፡ ልዩ ሃይሎችና አድማ በታኞችም ከፍጠኛ ቦታዎች ላይ በመሆን ሁኔታውን ለመቆጣጠር ቢሞክሩም ብሶት ወልዶት መንገድ ላይ የወጣውን የተጨቆነ ማህበረሰብ ግን ፈፅሞ ሊቆጣጠሩት አልቻሉም፡፡ ሙስሊሙ አሁንም ድረስ መንገዶችን በመዝጋት ተቃውሞ ላይ እንደሆኑለማዎቅ ተችሏል፡፡ እስካሁን 3 ወንድሞቻችን በደጋን ከተማ እንደተያዙ ምንጮች ገልፀዋል፡፡


ጨፋሮቢት ጀምሮ ደቡብ ወሎ ዞን እየተባሉ መጠራታቸውን ይጀምራሉ ፣ጨፋሮቢት ከሚሴ ፣ሃርቡ ፣ወለዲ ፎንተኒና ፣ኮምቦልቻ እንዲሁም ራቅ ብለው የሚገኙት ደጋን እና ገርባን ጨምሮ ደሴ እና ሌሎችም አጎራባች አገሮችንም እንደዚያው ጥሪያቸውን በደቡብ ወሎ ከተሰየመ ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በሰላማዊ ተቀምጠው እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን ባለፈው አመት የተጀመረውን የሙስሊሞች የተቃውሞ ሰልፍ መውጣት እና የመጅሊሱ በሙስሊሙ ማህበረሰብ መመራት አለበት መንግስት እጁን ከሃይማኖት ስር ያውጣ የሚሉትን ጥያቄዎች አስመልክቶ ምንም ነገር ድምጻቸውን ሳያሰሙ መክረማቸው ይታወሳል ።ሆኖም ግን ያደፈጡበት ዋነኛ አላማ ይኖረዋል ተብሎ ግምት ተሰጥቶታል ይላል የማለዳ ታይምስ የፖለቲካል አናላሲስት ሲጠቁም ዛሬ ባልታሰበ ወቅት ድንገት ወጥተው መንገድ መዝጋት የቻሉበት ዋነኛ ምክንያት ለለውጥ ፍለጋ እንደሆነ እና ይህም ሃይላቸውን አጠናክረው እንደመጡ የሚያሳይ ነው ፤የወሎ ሰው ካልደረስክበት አይደርስብህም ነገር ግን እልህ አስጨራሽ የሆነ ነገር ላይ ከደረሰ እና ትእግስቱ ካለቀ አትመለሰውም ያለው ይሄው አናላሲስት ምናልባትም ከማይወጡት አዘቅት ውስጥ የገቡትን የወያኔ አባላቶች ትእቢቶቻቸውን ሊያስተነፍሱ ይሆናል የወጡት ሲል ገልጾአል ።በትላንትናው እለት መንገድ ዘግተው ከ4 ሰአታት በላይ ሲጮሁ የነበሩት እነዚሁ የሙስሊሙ ህብረተሰቦች ድምጻችን ይሰማ የማይሰማ ከሆነ እና ተግባራት ላይ የማይውሉበት ነገር ከተፈጠረ እኛም ከአላማችን ፈቀቅ አንልም በማለት ለዞኑ አስተዳደር የገለጹ ሲሆን የመወሰኛ ደብዳቤም መላካቸውን ከስፍራው የደረሰን ሪፖርት ያመለክታል ።የዞኑ መስተዳድር ምንም ምላሽ ሳይሰጥ የሰልፉን መበተኛ ሰራዊት ቢልክም ሰራዊቶቹ ሊገድቧቸው እንዳልቻሉ እና መንገዶቹን ሁሉ በመኪኖች እና በድንጋይ አጥረዋቸው ስለነበር በምንም መልኩ አልፈው ጥቃት ሊፈጽሙባቸው እንዳልቻሉ ሰኢድ ዋርሶ የተባለው የፌስቡክ አባላችን ለማለዳ ታይምስ በላከው ሪፖርት ላይ ጠቁሞአል።
source maleda times.

1 comment: