
Asmelas Woldeselassei
ሆኖም ከአገር ቤት ያገኘነው ተጨማሪ ዜና እንደሚያመለክተው ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሏል። ትላንት እሁድ ከጠዋት ጀምሮ፤ ቤቱ በፌዴራል ፖሊሶች ተከቦ የነበረ ሲሆን፤ አመሻሽ ላይ በፖሊሶች መወሰዱን ለማወቅ ችለናል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋይ የተባለችው የህወሃት አባል እና በቁጥጥር ስር ውላለች። ግለሰቧ የታሰረችው ከጥቂት ቀናት በፊት የታሰረው የባለቤቷን አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ መረጃዎችን በማሸሽ በመደበቋ መሆኑ ተገልጿል።
ግለሰቦችን በሙስና የማሰር ሂደቱ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ፤ በተለይ ግልጽ ሌብነት ውስጥ የገቡት እና ንብረታቸውን ለማስመዝገብ አሻፈረኝ ያሉት ወ/ሮ አዜብ መስፍን፣ ጄነራሎቹ እና ሌሎች የህወሃት ሰዎች አስጊ ሁኔታ ውስጥ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
No comments:
Post a Comment