No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Friday 8 February 2013

በብዙ መቶሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ዋሉ

የካቲት ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-<<ጅሀዳዊ ሀረካት>> የተሰኘውንና በ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሰሞኑን የተላለፈውን ፊልም በመቃወምና ለታሰሩት የሙስሊም መፍትሔ =  አፈላ ላጊ ኮሚቴዎች አጋርነታቸውን ለመግለጽ በብዙ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ዛሬ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲያሰሙ ውለዋል።
“መሪዎቻችን ይፈቱ! ዓላማችን ኢስላማዊ መንግስት ሳይሆን የሀይማኖት ነፃነታችንን ማግኘት ነው! ድምፃችን ይሰማ ፣ በዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ይቁም>>የሚሉ እንዲሁም የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንን የሚያወግዙ መፈክሮች ቀርበዋል።
በተቃውሞው ላይ የተሳተፈ አንድ ሙስሊም፣  ተቃውሞው መስሊሙ ለመሪዎቹ ያለውን ድጋፍ በቁርጠኝነት የገለጠበት ነበር ብሎአል።
<<ጅሀዳዊ ሀረካት>>በሚል ርዕስ በ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የተለቀቀው የፈጠራ ድራማ በሙስሊሞች ብቻ ሳይሆን በሌሎች እምነት ተከታዮች፣በተቃዋሚ ፓርቲዎች እና በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ጭምር ከፍ ያለ ተቃውሞና ውግዘት እየቀረበበት ይገኛል።

No comments:

Post a Comment