No one is born hating another person because of the colour of his sikn, or his background or his religion.
People must learn to hate, and if they can learn to hate, they can
be tought to love, for love comes more naturally to the human heart than its opposite. Nelson Mandela.

Friday 28 September 2012

በደሴ ከተማ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተከናወነ !ዘግይቶ በደረሰን ዜና መሰረት ደግሞ በአንዋር መስጊድ ከፍተኛ የህዝብ ብዛት ያለው ሰው ተቃውሞውን ሲያሰማ እንደዋለ ተጠቁሞአል ።


በደሴ ከተማ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ተከናወነ
ከስምንት ወር በላይ የያዘው የእስልምና ተከታዮች ይሄው የድምጻችን ይሰማ ፣የምንፈልገውን እኛው እንመርጣለን መንግስት በሃይማኖቶች ጉዳይ ጣልቃ አይግባብን የሚለው ጥያቄ አሁንም እንደቀጠለ ዉሏል በዛሬው ዕለት በደሴ ከተማ ከፍተኛውን የተቃወሞ ሃሳባቸሃንውን ሲያሰሙ የዋሉ ሲሆን ከባለፈው ሳምንት በተሻለ መልኩ ድምጻቸውን ለማሰማት እንደቻሉ ሪፖርተራችን ያሬድ ከስፍራው ዘግቦአል ።የባለፈውን ሳምንት የፌደራል ፖሊሶች በንጹን ዜጎች ላይ ያደረሱትን ዘገባ ጠቅሶ ሁለት ወጣቶች በከፍተኛ ደረጃ ከመደብደባቸውም በላይ በአሁን ሰአት አንደኛው በደሴ ሆስፒታል በህክምና ላይ ሲሆን አንዱ ግን የደረሰበት አልታወቀም ሲል በዘገባው ላይ ገልጿል።በተመሳሳይ ዜና ሲገልጽ በነዚህ ወጣቶች ላይ የተፈጸመው ድብደባ ሰበአዊነት እና ርህራሄ የጎደለው ከመሆኑም በላይ ራሳቸውን ስተው መንገድ ላይ ለሁለት ሰአታት ሲደበድቧቸው ተመልክቼአለሁ ከዚያም በኋላ በፖሊስ መኪና ጭነዋቸው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋቸዋል እኔም ሪፖርቴን ለማጠናቀር ስል ተከታትዬ ብሄድ ከፖሊስ ጣቢያው ሊያደርሱኝ ባለመቻሌ ያሉበትን ለማወቅ አልቻልኩም ነበር ሲል የጠቆመ ሲሆን ነገር ግን ከተደብዳቢዎቹ ወገን የሆነ አንድ ጓደኛው ወዳጁ የት እንደአለ ጠቁሞኝ በትላንትናው እለት ሆስፒታል ሄጄ ጠይቄዋለሁ ደህንነቱ በከፋ ሁኔታ ላይ ነው ሲል ገልጾ ስለሌላኛው ወገን ግን ምንም ነገር የተሰማ ፍንጭ የለም ጓደኛውንም ስጠይቀውም የማውቀው ነገር የለኝም በማለት በሚያቃስት እና በደከመ ድምጽ ገልጾልኛል ሲል የማለዳ ታይምስ ዘጋቢ ያሬድ ከስፍራው ዘግቦአል።
ዘግቦአል።በተለይ በአዲስ አበባ ከግማሽ፡ሚሊዮን የሚበልጡ ሙስሊም ኢትዮጵያውያኖች መዲናይቱን አዲስ አበባን በሃይማኖት የነጻነት ጥያቄ ህገመንግስታዊ መብታችን ይከብረልን በሚሉ የጀመሩትን ትግል በማጠናከር ድምጻቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያስረዳል። ይህን ተከትሎ በጅማ በደሴ በአርሲ በሃረር በአንቦ ከተማ ለሃይማኖታቸው ነጻነት መከበር የሚያከሂዱት ትግል ቀላል እንዳልሆነ በመጥቀስ መንግስት እንደ ሃገር መሪነቱ መልስ እስኪሰጠን ጥያቄያችንን በጀመሩት ሰላምዊ መንገድ እንደሚቀጥሉ የገለጹ አንዳንድ የሰላዊ ትግሉ ተሳታፊ ሙስሊም ወገኖቻችን ምናልባት የመንግስት ምላሽ እኛ እያደረግን ካለው እንቅስቃሴ አንጻር በተቃራኒው ከሆነ ማንኛውንም መስወአትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምርጫችን በመስጂዳችን በሚል መሪ መፈክር የታጀቡ ሙስሊም ወገኖቻችን በመንግስት ላይ ያላቸው ተስፋ የቱንም ያህል የጨለመ ቢሆንም በፈጣሪ ሃይል ይህ ስረአት ተፍረክርኮ ለህዝበ ሙስሊሙ ሰላምዊ ጥያቄ አፋጣኝ እና አወንታዊ መልስ የሚስጥ፡ሃገር ወዳድ እና ህዝባዊ መንግስት ወደ ስልጣን መጥቶ ጥያቄ ያችው የሚፈታበት ግዜ እሩቅ እንደማይሆን እምነታቸውን ገልጸዋል።
በአንዋር መስጊድ
በተለይ በአዲስ አበባ ከግማሽ፡ሚሊዮን የሚበልጡ ሙስሊም ኢትዮጵያውያኖች መዲናይቱን አዲስ አበባን በሃይማኖት የነጻነት ጥያቄ ህገመንግስታዊ መብታችን ይከብረልን በሚሉ የጀመሩትን ትግል በማጠናከር ድምጻቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያስረዳል። ይህን ተከትሎ በጅማ በደሴ በአርሲ በሃረር በአንቦ ከተማ ለሃይማኖታቸው ነጻነት መከበር የሚያከሂዱት ትግል ቀላል እንዳልሆነ በመጥቀስ መንግስት እንደ ሃገር መሪነቱ መልስ እስኪሰጠን ጥያቄያችንን በጀመሩት ሰላምዊ መንገድ እንደሚቀጥሉ የገለጹ አንዳንድ የሰላዊ ትግሉ ተሳታፊ ሙስሊም ወገኖቻችን ምናልባት የመንግስት ምላሽ እኛ እያደረግን ካለው እንቅስቃሴ አንጻር በተቃራኒው ከሆነ ማንኛውንም መስወአትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል። ምርጫችን በመስጂዳችን በሚል መሪ መፈክር የታጀቡ ሙስሊም ወገኖቻችን በመንግስት ላይ ያላቸው ተስፋ የቱንም ያህል የጨለመ ቢሆንም በፈጣሪ ሃይል ይህ ስረአት ተፍረክርኮ ለህዝበ ሙስሊሙ ሰላምዊ ጥያቄ አፋጣኝ እና አወንታዊ መልስ የሚስጥ፡ሃገር ወዳድ እና ህዝባዊ መንግስት ወደ ስልጣን መጥቶ ጥያቄ ያችው የሚፈታበት ግዜ እሩቅ እንደማይሆን እምነታቸውን ገልጸዋል። በዛሬው እለት የዋለው ይሄው ተቃውሞ የአዲሱን ጠቅላይ ሚንስትር ያሉበትን ደረጃ ምን እንደሆነ በግልጽ ያሳያል ይላሉ ይህንንም አጠንክረው ሲገልጹ እሳቸው አማኝ እንደመሆናቸው መጠን የሌሎችንም የእምነት መብት ሊቃወሙ እንደማይችሉ እርግጥ ነው ስለዚህ መብታችንን ይለግሱን እና መፍትሄ እንሻለን ብለዋል

No comments:

Post a Comment